Thursday, March 17, 2016

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ካምፓስ የተማሪዎች መኝታ ክፍል ተኩስ ተከፈተ

በጅማ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ካምፓስ ተማሪዎች ተቃውሞ ማሰማታቸውን ተከትሎ በሕወሓት ወታደሮች በቅጥር ጊቢውና በተማሪዎች መኝታ ክፍል ተክስ መክፈታቸው ተሰማ::
ከአካባቢው  የደረሱ መረጃዎች እንዳመለከቱት ኦሮሚያን በ8 ዞኖች ከፋፈለው ከሚመሩት የሕወሓት የመከላከያ ሰዎች መካከል የሆኑት ወታደሮች በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው የደረሰን መረጃ አመልክቷል::
እንደ ዓይን እማኞች ገለጻ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ካምፓስ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል:: በርካታ ተማሪዎች በጥይት እና በደረሰባቸው ቅጥቀጣ ተጎድተዋል::
Haregeweyn Abeje's photo.

No comments:

Post a Comment