ስለኩዌት መረጃውን ያገኘሁት ግሩፕ ውስጥ ስገባ ነው። ኤልዳና ፖስታዋለች አነበብኩት። ይጠቅማል እሰራለሁ ትንሽ ለውጥ አገኛለሁ ብሎ ለሚያስብ ጥንቃቄ ይሻል። ወደው ከኮንትራት ቤት አልጠፉ..
ኩዌት ውስጥ የምትገኙው ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ኤርትራውያን ራሳችሁን ጠብቁ የኩዌት መንግሥት የተለያዩ ሀገር ዜጋዎችን መንገድ ላይ በማስቆም ፍተሻ እያረገ ነው። ፓስፖርታቸው ያልታደሰ በህገ-ወጥ መንገድ የገቡ እንዲሁም ከዚይ በፊት በተለያየ ነገር የተጠረጠሩ… እንዲሁም ህጋዊ ያልሆኑትን በማሰር ወደ ሀገራቸው እንመልሳለን ብለው ፍተሻውን አጡፈውታል
የመኖሪያ ወረቀት ያላችሁም ስትንቀሳቀሱም ፓስፖርታችሁን መያዝ አትርሱ። በተለይ ግን ተገፍታችሁ እና መከራ ሆኖባችሁ ከኮንትራት ቤት ወጥታችሁ ፓስፖርት እጃችሁ ላይ የሌለ ፓስፖርት ኖሯችሁ መኖሪያ ፍቃድ የሌላችሁ አብዝታችሁ ጥንቃቄ አድርጉ።
ኢትዮጵያውያን ሰንት እንደተያዘ ባይታወቅም ፎቶው ላይ እንደምትመለከቱት ስደተኞች ናቸው። ክፉውን ያርቅልን።
አሜን!!!!!


No comments:
Post a Comment