Friday, March 11, 2016

ሰበር ዜና ! ! የኢትዮ ቴልኮም እና የብሐራዊ መረጃ ጋብቻ!!


የህወሃት የገቢ ምንጭ የሆነዉ የኢትዮ ቴልኮም ድርጅት ከዚህ ቀደም ከብሄራዊ መረጃ ጋር የነበረዉ የመሐበራዊ መገናኛ ድህረ ገጾችን የማፈንና የመሰለል ዘዴ አጥጋቢ ዉጤት ባለማምጣቱ ! ምክንያት…
በመላዉ ሐገሪቱ ላይ የህዝብ አመጽ ለመቀስቀሱና ለመበራከቱ አይነተኛ መንገድ ነዉ ተብሎ በህወሃት ወልጀለኛ አምባገነኖች በመታመኑ ሰበብ !! በሞባይል ስልኮችና በተቀማጭ ኮምፒዉትሮች አማካኝነት ይሰራጫሉ የተባሉ በተለይም እንደ ፌስ ቡክ እና ቫይቨር እንዲሁም የመሳሰሉትን ለማፈንና ለማኮላሸት አዲስ ዘዴ ቀይሶ ተንቀሳቅሷል።
በመሆኑም በብሄራዊ መረጃ ዉስጣዊ መዳፍ ስር የሚገኘዉ ኢትዮ ቴልኮም ወያኔያዊ ድርጅት ከፌብሯሪ 23/2016 ጀምሮ እስከ ማርች 1/2016 የድርጅቱን አቅም የማሳደግ ስራ በሚል ሰበብ አዲስ የመሓበራዊ ገሶችን የስለላ ሶፍት ዌር መግጠሙን ታማኝ መረጃዎች የጠቆሙ ሲሆን !!
በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባና በሌሎችም ብዛት ባላቸዉ የሐገሪቱ ክፍሎች የቫይቨርና የፌስ ቡክ እንዲሁም የመሳሰሉት አገልግሎቶች በመረጃ ድርጅቱ ትእዛዝ መሰረት ከትናንትናዉ እለት አንስቶ በስብጥር እንዲዘጉ ተደርጓል ።
በመሆኑም ቀደም በዋልታ የዜና ማሰራጫ በኩል የቴልኮም አገልግሎት የሞባይል የታሪፍ መጠንን በመቀነስ ወይም የአገልግሎት መጠንን በማስፋት መልኩ ( Ethio telecom announces a broad mobile internet service tariff revision and new mobile internet service packages starting from February 23, 2016. )
( ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎትን ለማበረታታትና እንዲሁም የኢንተርኔት አጠቃቀም ባህልን በሃገራችን እንዲጎለበት ለማድረግ የሚረዳ የሞባይል ኢንተርኔት የታሪፍ ቅናሽ ያደረገ ሲሆን ማሻሻያው ከየካቲት 15 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል፡ )
እንዲለፈፍ ተደርጎ የተነገረው የማደናገር ዜና!!….. የማህበራዊ የመገናኛ አዉታሮችን ለማፈን እንዲረዳ ታልሞ ታቅዶ የነበረ ሲሆን…. ከአለም አቀፍ የፌስ ቡክ ህግና ደንብ መሰረት! በወያኔና በቻይናዊያን ሃከሮች የታሰበዉ ሴራ መክሸፉን ምንጮቻችን አሳዉቀዋል።
ይህን ተንተርሶ አዲስ የተገጠዉ የጠለፋ ሶፍት ዌር በደረሰበት የፌስ ቡክ እገዳ መሰረት በኢትዮ ቴልኮም ላይ የሞባይል ግንኙነት ዘዴ አገልግሎት ዉስጥ ከፍተኛ ችግር ተፈጥሯል! በዚህ የተነሳ ከትናንትናዉ እለት ጀምሮ ይህዉ የፌስ ቡክ፣ የቫይቨርና የመሳሰሉት አገልግሎቶች በብሔራዊ መረጃ ትእዛዝ መሰረት እንዲቋረጥ በመደረጉ በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚደርስ ብዙሃን እየተናገሩ ይገኛሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ
( ጉድሽ ወያኔ )
Gudish Weyane's photo.

No comments:

Post a Comment