ስለ ፎቶዎቹ ምንነት ባጭሩ ላስቀምጥ
ተደብዳቢው አማራ
ደብዳቢው ወያኔ ትግሬ
የድብደባው ምክንያት አማራ መሆን
ተጠያቂ የለም
ይህንን ለማስቆም የሚቆም አማራ የለም
ደብዳቢው ወያኔ ትግሬ
የድብደባው ምክንያት አማራ መሆን
ተጠያቂ የለም
ይህንን ለማስቆም የሚቆም አማራ የለም
ይህንን ኣይቶ ቁጭት ውስጥ ሊገባ የሚችል አማራ የለም
ድብደባው ይቀጥላል ወይ ኣዋ!
ድብደባው ይቀጥላል ወይ ኣዋ!
ይህንን ፎቶ ለብዙ ደቂቃ ተመለከትኩት ። ኣይኖቼ እንባ ተሞልተው ጥርሴን እያፋጨሁ ደግሜ ደጋግሜ ኣየሁት። ወዳጄ በውስጥ መስመር የፃፈልኝን ኣሳዛኝ ታሪክም ኣነበብኩ ። ማልቀስ ኣልችልም ፥ ኣሁንም ያለቀስኩ ኣይመስለኝም ፥ ግን ፊቴ ላይ እንባ የሚመስል ነገር እንደነበር ኣስታውሳለሁ ። መናደድም ኣልፈልግም ፥ ምክንያቱም ከመናደድ የሚመጣው ሽንፈት እንደሆነም ኣውቃለሁ ። ግን ማሰብ እፈልጋለሁ ፥ ድጋሚ ወደ ራሴ ተመልሼ እውነታውን በጥሞና ማየት እና መረዳት እፈልጋለሁ ።
በቃላችን መሰረት የወዳጄን ምንነትም ሆነ ማንነት ለመናገር ኣሁን ጊዜው ኣይደለም ። ግን ይህ ድብደባ ምን ማለት እንደሆነ ላስረዳ።
በቃላችን መሰረት የወዳጄን ምንነትም ሆነ ማንነት ለመናገር ኣሁን ጊዜው ኣይደለም ። ግን ይህ ድብደባ ምን ማለት እንደሆነ ላስረዳ።
ብዙ ለአማራ የሚጮህ ፥ እቆጫለሁ ባይ እኔ ባለሁበት ኣማሪካ ይኖራል ። እጅግ ብዙ ነገር ማድረግ የሚችል ኣቅም ያለው አማራ በየ ሃገሩ እንደሚኖር ኣውቃለሁ ። ትንታግ የሆኑ ፥ በሳል እና ብልህ አማሮች። ግን ደሞ ኣቅማቸውን የማያውቁ ፥ ከስብሰባ እና ጥናታዊ ፅሁፍ ከማቅረብ ውጪ እኔ እስከማውቀው ድረስ ኣንድ እርምጃ ወደፊት መራመድ ያልቻሉ መሆናቸውን ሳስብ ይገርመኛል። ነፃነት እና የኣማሪካ ህግ የተቀላቀለባቸው ተቆጪዎች በመሆናቸው ፥ ይቆጡና ግን መራመድ ይፈራሉ ፥ ይናደዱና ግን መተግበርን ይሰጋሉ ፥ ይበሳጩና ግን መሆንን ይሸሻሉ ። በመሆን እና ባለመሆን መሃከል የቆሙ ተቆርቋሪዎች ስለሆኑ ፥ ወገኖቻቸው ዛሬም ይደበደባሉ ፥ ይታሰራሉ ፥ ይታረዛሉ ፥ ይገደላሉ ። በመራመድ እና በመቆም መሃል ስላሉ ፥ ወገኖቻቸው እያለቁ ነው ። ይህም ፎቶ የነዚህ የኣማራ ልሂቃን ውሳኔ መዘግየት ውጤት ነው ። ሃያ ኣምስት ኣመት ለመራመድ የከበደን ፥ ሃያ ኣምስት ኣመት ቀና ለማለት የከበደን በውሳኔና በፈረንጅ ሃገር ህግ መሃል ስለቆምን ይመስለኛል ።
ኣማሪካንን ሳስብ የህግ ሃገር ነች ። የነፃነት ሃገር ነች ። የሰዎች መብት የሚከበርባት ሃገር ነች ። ይህ ሁሉ እውነት የሚሆነው ግን በመጀመሪያ ከማንም በላይ ለኣማሪካኖች እና ኣማሪካ ውስጥ ለሚኖሩ ህዝቦች ነው ። ኣማሪካ ከኣማሪካ ውጭ ሁል ጊዜ ልክ ነች ብዬ የማስብ እብድ ግን ኣይደለሁም ። ለምሳሌ ፕሬዝዳንት ኦባማ ኢትዮጵያ በሄደ ጊዜ የኢትዮጵያ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ነበር ሲል ተሰምቷል ። ምርጫው ፍትሃዊ ስለነበረ ነው ? ኣይደለም ! ኦባማ መረጃ ስለሌለው ነው ? ኣይደለም ! ዋነኛ ምክንያቱ ለኣማሪካ ልክ የሚሆነው ኣባባል ምርጫው ፍትሃዊ ነው የሚለው ኣባባል ብቻ ስለነበረ ነው ። ኣማሪካ ውስጥ ስኖር የኣማሪካን ህግ ኣክብሬ መኖር እሻለሁ ማለት የኣማሪካ መሪ የኢትዮጵያዊያኖች ስቃይ ቸል ብሎ ሲያልፈው እቀበላለሁ ማለት ኣይደለም ። ኣማሪካን ሃገር መስረቅ ያሳስራል ። ኦባማን መተቸት ግን ኣያሳስርም ። ለነፃነት መታገል ግን ኣያሳስርም ። ቢያሳስርም ታግዬ እታሰራለሁ እንጂ ፈርቼ ዝም ኣልልም ። ከዚ በባሰ እና በተወሳሰበ ደረጃ ባንድ ጎን ለኣማሪካ ህግ ተገዥ ለመሆን ኣስበን ፥ በልላ ጎን ደሞ የህዝባችን ስቃይ ኣስቆጭቶን ፥ ፍርሃት እና ውሳኔ ተጋጭቶብን ስለመቆማችን መካዳችን ይመስለኛል ለውጥ እንዳናመጣ ያደረገን ። የኣማሪካ ህግ ንፁሃን ዜጎች ይገደሉ የሚል ኣይመስለኝም ፥ የሚል ከሆነ ግን ኣላከብረውም ፥ የኣማሪካ ህግ የኣማሪካ መንግስት የተሳሳተ መረጃ እንዲናገር ፍቃድ ኣይሰጠውም፥ የሚሰጠው ከሆነ ግን በእንደዚህ ኣይነቱ ህግ ኣልገዛም ፥ የኣማሪካ ህግ ሰዎች በዘራቸው ተቆጥረው እና ተጠርተው ሲገደሉ በማየታችንን ይህንን ለማስቆም ማንኛውም ኣይነት ትግል ውስጥ ብንገባ እና ጉዳዩን እንደ ኣንድ መንግስት ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ ገዳዮቹን እያወደሰ « ምንም የተፈጠረ ነገር የለም !» ቢለኝ ፥ ኣሁንም እንዲህ ኣይነቱን ህግ ኣላከብርም ። እኔ በግሌ ህግ ከማይከበርበት ገነት ፥ በህግ የሚተዳደር ገሃነምን እመርጣለሁና።
ምን ለማለት ነው ፥ ኣማሮች የቱን ትመርጣላችሁ ? እንዲህ ብናደርግ ኣማሪካ እንዲህ ብታደርገንስ የሚለውን ፍርሃት ወይስ የማደርገው ነገር ህጋዊ ነው ፥ ለሰው ልጆች መብት የመቆም ትግል ነው ፥ የነፃነት ጥያቄ ነው በሚለው ላይ ኣምኖ ከፓናል ዲስኩር እና ከረባት ኣስተካክሎ ለማውራት ፥ ከመጨቃጨቅ እና ከመጠቋቆም ይልቅ ህዝባችሁን በቁርጠኝነት ከመከራ ለመታደግ ትግል መታገል ? ህዝቡ ትግል ይፈልጋል ፥ ህዝቡ እናንተን ያያል ፥ የህዝቡ በትረ ሙሴ ለመሆን ግን ፥ በማንነት እና በፍርሃት መሃል ከመቆም ነፃ መውጣት ያስፈልጋል ።
የኣማራ ደም በከንቱ ፈሶ ኣይቀርም !
ሄኖክ የሺጥላ




No comments:
Post a Comment