Thursday, March 10, 2016

በአዲስ አበባ ክባድ የመኪና አደጋ ደረሰ የ6 ሰው ህይወት ቀጥፋል



በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 10  በተለምዶው ሰሚት  በሚባለው አካባቢ በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ::
የአካባቢው ነዋሪዎች በፎቶ ግራፍ አስደግፈው  በላኩት መረጃ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ሰሚት የለስላሳ መጠጦች ፋብሪካ አካባቢ በሚገኝ መስቀለኛ መንገድ ላይ ሲኖ ትራክ መንገድ ስቶ ከመንገድ ጋር ሲጋጭ ግንብ በመፍረሱ በአቅራቢያው ሰው አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ባጃጅ መኪና ላይ በመውደቁ አሽከርካሪውን ጨምሮ ተሳፋሪዎች ሕይወታቸው አልፏል::  ከሟቾች መካከል ሁለቱ ሴቶች መሆናቸውም ታውቋል::: ፖሊስ የአደጋውን ሁኔታ እያጣራ ይገኛል:: በዚህ አደጋም በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ተሰምቷል::

No comments:

Post a Comment