Monday, March 21, 2016

የህወሃት ወታደራዊ ሰላዮች ወደ ኤርትራ ዘልቀው ሊገቡ ሲሞክሩ መረሸናቸው ተነገረ


በኤርትራ እና በዙሪያዋ ለስለላ ስራ እንዲሁም ለቃኘዉ የዉጊያ ስምሪት እንዲጠቅሙ ተብለዉ የተሰማሩ የህወሃት ወታደራዊ መረጃ ሰራተኞች እየታደኑ መታፈናቸዉን የሚያረጋግጡ መረጃዎች አፈትልከዉ ወጥተዋል።
በተልይም ሞላ አስገዶም ከኤርትራ ወደ ህዉሃት ከፈረጠጠ ወዲህ በኤርትራ እና በነጻነት ሐይሎች የደህንነት ክትትል ምክንያት በህወሃት መረጃ ሰንሰለቱ ስር የነበሩ ሰላዮች በሙሉ መረሸናቸዉን የወያኔ ወታደራዊ ደህንነት በማረጋገጥ ለመከላከያ ሚኒስቴሩ እና ለሚመለከታቸዉ የደህንነት ክንፎች አሳዉቋል።
ወታደራዊ ደህንነቱ ሌሎች በተለያየ ምክንያት ወደ ኤርትራ ሰርገዉ እንዲገቡ የተደረጉ የስለላ ሰዎች በተለይም የአርበኞች ግንቦት ሰባትን አጠቃላይ ፖለቲካዊና መሰረታዊ የአደረጃጀት እርከን፣ እንዲሁም ወታደራዊ ኮርሶችና ዲስፕሊኖችን፣ ስልታዊ መዋቅርንና አቀማመጥን ለመሰለል እንዲረዱ ከተሰማሩ ግለሰቦች ዉስጥ አንዳቸዉም የት እንደገቡ ለማወቅ ያለመቻሉን ምንጮቻችን ጠቅስዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ዉጊያዉ አምድ ከተቀላቀሉ ወዲህ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ በፍጥነት እየአሰገሰ በመምጣት ላይ የሚገኘዉን የለወጥ ነዉጥ መቛቋም የተሳነዉ የትግራይ ነጻ አዉጭዉ ቡድን ወታደራዊ ደህንነት የአርበኞች ግንቦት 7ን እና የጥምር ሐይሎችን እንቅስቃሴ ማወቅ እንኳ እንደተሳነዉ የደህንነት ስልቱም መበለጡን በተለይም የተሳሳቱ መረጃዎች እየደረሱት ላም ባልዋለበት!! ሲቅበዘበዝ የነጻነት ሐይሎቹ ሽምቅ ዉጊያ ሰለባ እየሆነ መምጣቱን ለተደራቢ አዛዡ ሉተናንት ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል በማቅረብ የተወያየ ሲሆን።
ስርአቱ አሁን ባጋጠመዉ የመረጃ መዳፈን ምክንያት ስጋት ላይ ስለወደቀ ድንገተኛና የተጠናከረ ተመላላሽ ጥቃት እንዲሰነዘር እንዲሁም በጎንደር ዙሪያ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት በእጅጉ እንዲጠናከር ለማድረግ ከሸዋሮቢት የመጡ አዲስ ወታደሮች ወደ ክፍለ ጦሮች እንዲካተቱ እና አጥቂዉ የግንባር ሐይል ለመመሪያ ዝግጁ እንዲሆን በአመራሮች ቢወሰንም ከተራ ወታደር አንስቶ እስከ ከፍተኛ አመራሮች መመሪያ ለመቀበል ስጋት ላይ ናቸዉ።
ይህን መረጃ አያይዘዉ የላኩልን ምንጮች በኤርትራ የሚገኙ የነጻነት ሐይሎች ከምንዜዉም በበለጠ በንቃትና በመጠናከር እየወደቀ የሚገኘዉን ባለ ሁለት እግር ዝሆን ለመጣል እንዲዘጋጁ መዘናጋትን ፈጽመዉ እንዳያስቡት አስጠንቅቀዋል።
ከአራት እግሮቹ ሁለት የፊት እግሮቹን የቆሰለ ዝሆን ለመጣል ዝሆን መሆን አያስፈልግም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

No comments:

Post a Comment