በኢትዮጵያ አንድ ነጋዴ እስር ቤት እንዳለው ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም በግልፅ ተናግረዋል። ቱጃሩ ዛሬ ጡንቻው እንዲፈረጥም ጥርጊያ መንገድ ያመቻቹት በስልጣንና እስር ቤት ይገኛሉ። የደህንነት ሹም ወ/ስላሴና የጉምሩክ ሃላፊ ገ/ዋህድ እንዲሁም በረከት ስሞኦንና አዜብ መስፍን ይጠቀሳሉ። 200 ነጋዴዎች በቱጃሩ ትእዛዝ በጉምሩክ ግቢ በኮንቴነር ውስጥ እንዲታሰሩ ያደረገው ገ/ዋህድ (የተጠቀሱት ባለስልጣናት ተባብረዋል) ድብደባ ይፈፅምባቸው ነበር። ፍ/ቤት ፍታ ሲለው አንፈታም ብሎ በአደባባይ ተናገረ። ከታሳሪዎቹ በድብደባ ጆሯቸው ይመግልና ይሰቃዩ እንደነበር ቢገልፁም ሰሚ አልተገኘም፤ የፍ/ቤት ውሳኔ አልተከበረም። 2 ነጋዴዎች የገዛ ህይወታቸውን እንዲያጠፉ ተደርጓል። የሪፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ በመፃፉ ብቻ በጠራራ ፀሀይ የግድያ ሙከራ ተፈፀመበት። ድርጊቱን የፈፀሙ በቦሌ የሸኙት በረከትና ወ/ስላሴ ነበሩ። በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከባንክ ቱጃሩ እንዲበደሩ ፍቃድ ሲሰጡ የቆዩት በረከት ናቸው። ..ብዙ ማስረጃና መረጃ ማቅረብ ይቻላል። ቢዘገይም ጠ/ሚ/ሩ ሀቁን አፍርጠዋል፤ እርምጃ ባይወሰድም! በአንፃሩ በቀለ ገርባ፣ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አብርሀ ደስታና ሌሎች ንፁሀን “ህግ ይከበር! መናገርና መፃፍ መብት ይጠበቅ! ግድያና እስር ይቁም!” ብለው በሰላማዊ መንገድ በመጠየቃቸው ከነወ/ስላሴ ጋር እስር ቤት እንዲማቅቁ ተደርገዋል። ሃ/ማርያም ዛሬ ያመኑትን ጉዳይ እነዚህ ወገኖች ለአመታት ሲጮሁበት ከርመዋል። ..ነጋዴው የእግር ኳስ ክለብ ከማፍረስ እስከ እስር ቤት ማቆም ደረሰ።ነገ ደግሞ መንግስት ላለማቆሙ ማረጋገጫ የለም። ለነገሩ እስር ቤት አስቀድሞ ማቆሙ ..

No comments:
Post a Comment