የአገሪቷ ህዝብ ከዳር እሰከ ዳር ባለው አገዛዝ ተገፍግፎ እንዴት ከዚህ አገዛዝ ነፃ እንደሚወጣ ሌት ከቀን በሚማስንበት በዚህ ጊዜ ወያኔ እንዴት የስልጣን ዘመኑ ሊረዝም ቻለ ?
ዋነኛው ምክንያት አንድና ግልፅ የሆነ ነገር ነው የህዝቡን እሮሮ በመተራስ ተገን በማድረግ ስልጣን ላይ በአቋራጭ ቁጭ ሊሉ ያሰቡ ራሳቸውን ግን የተቃዋሚ ድርጅት ነን የሚሉ ቁጥር ስፍር የሌላቸው በጣም ብዙ ጎራዎች በመፈጠራቸው ዋነኛው ምክንያት ሆኖ መቅረብ ይችላል
በሰላማዊ መንገድም ሆነ ትጥቅ አንስተው በረሃ የወረዱት የፖለቲካ ድርጅቶች እውነት ከወያኔ የተሻለ አጀንዳ ያላቸው አይመስሉም ወያኔ ያደረገውን እሱም እየደገሙት ነው እንጂ ስለ አንድ አገር የሚታገሉ አይመሰሉም
እነዚህ ቁጥራቸው እንደ ከዋክብት የበዛ ድርጅቶች ለምን መታረቅንና በአንድ እቅፍ ስር ሆነው መታገሉን ጠሉ ?
ይህም ምክንያቱ ግልፅ ነው ዋናው አላማቸው የስልጣን ጥማትእና የወንበር ጉጉት ሰለሆነ ብቻ ነው
ይህም ምክንያቱ ግልፅ ነው ዋናው አላማቸው የስልጣን ጥማትእና የወንበር ጉጉት ሰለሆነ ብቻ ነው
በዚህም የተነሳ የአማራው ነገድ ትንሽ ከተሰባሰበና ከጠነከረ ወደ ስልጣን ወንበሩ አያስደርሰንም በሚል እሳቤ የአማራ መደራጀት በሁሉማ አቅጣጫ ለማክሸፍ ይጥራሉ
መልዕክቱ ለሁሉም የተቃዋሚ ( የወያኔ እድሜ ማራዘሚያዎች) ለሚሉት ጠቅላላ ነው
ምክንያቱም ማንኛውም ለአንድ አገር እየታገልኩ ነው የሚል ድርጅት ሌሎችን እንኳ ጨፍልቆ በስር ማድረግ ቢያቅተው እሱ ተጨፍልቆ አንድ አካል መሆን የማይችልበት ምንም ምክንያት ሊኖረው ባልተገባ ይህ እኮ ነው ለአገር የሚከፈል መስዋዕትነት
No comments:
Post a Comment