Saturday, March 26, 2016

ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ተቃዋሚዎች የወያኔን ኢንባሲ አስጠነቀቁ ! !


ደቡብ አፍሪካ በተለይም በጆሃንስበርግ የሚኖሩ የወያኔ ተቃዋሚዎች ላይ የትግራዩ ነጻ አዉጭ ቡድን ፕሪቶሪያ በሚገኘዉ ተወካዩ ኢንባሲ አማካኝነት ወንጀል ለመፈጸም ማሴሩን ከዉስጥ የወጣ መረጃ አመላክቷል።
በኢትዮጵያ ዉስጥ ሰባዊ መብታቸዉ ተገፎ በግፍ የሚወዷትን ሐገራቸዉን ጥለዉ በደቡብ አፍሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት ተሰጥቷቸዉ የሚኖሩት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በተለያየ ወቅትና ግዜ ህወሃት ወያኔ በሐገራችን ዉስጥ የሚፈጽመዉን ኢሰባዊ ድርጊት በመቃወም አደባባይ እየወጡ ድምጻቸዉን የሚያሰሙና የተለያዩ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ደጋፊዎች የሆኑ ስደተኞች ላይ በሙሰኛ ፖሊሶችና በዘራፊዎች የተደገፈ ዉንብድና ለመፈጸም እየተሞከረ መሆኑን ያነጋገርናቸዉ ስደተኞች አረጋግጥዋል፡፤
ለጊዜዉ ስማቸዉን መጥቀስ ያልፈለጉ ነገር ግን ተደጋጋሚ የጥቃት ሙከራ የተደረገባቸዉ አንድ ግለስብ ”
መኪና ሳሽከረክር በተደጋጋሚ ማንነታቸዉን የማላዉቃቸዉ ሰዎች ይከታተሉኛል አንዳንዴ ፖሊሶች ነን ብለዉ ያስቆሙኝና ዛቻና ማስፈራሪያም ይደርሰብኛል ለሚመለከተዉ አካል ሁሉ አመልክቼ እራሴን በመጠበቅ ላይ እገኛለዉ ”
ሲሉ ሌላኛዉ ደግም
” በመኪና ክትትሉ ተጠናክሮ ቀጥሏል የት እንደምንገባ የት እንደምንሄድ የት እንደምንዉል ሁሉ ለማወቅ የሚደረግ አይነት ነገር ነዉ እኛ አንፈራም ሐገራችንን ወስደዉብናል እዚህ ደቡብ አፍሪካ በኛ በተቃዋሚዎች ወገን በሚገኝ አንድ ግለሰብ ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ማን እንደሚጎዳ ያዉቁታል እያንዳንዳቸዉ የወያኔ ሰላዮች እንዲሁም ደጋፊዎች የኢንባሲዉ ሰራተኞች አምባሳደር ሙሉጌታን ጨምሮ ከሰኒ ሳይድ እስከ ሜለን የት እንደሚኖሩና የት እንደሚዉሉ እናዉቃለን መድረስ ያለብን ቦታ ሁሉ ደርሰናል እንደርስማለን አሁንም በስደት ተጠልለን በምንኖርበት ሐገር ላይ እንዲህ ያለ ተልካሻ ዉንብድናቸዉን በመላዉ አለም ላይ የምትገኙ ወገኖቻችን በሙሉ ተገንዝባችሁ በማንኛዉም መልኩ ለሚደርስብን አደጋ ቀጥታ ተጠያቂዉ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ፕሪቶሪያ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኢንባሲ መሆኑን እያስገነዘብን እራሳችንን ለመከላከል ማንኛዉን አይነት ዝግጅት ያደረግን ምሆኑን እናሳዉቃለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )
Gudish Weyane's photo.

No comments:

Post a Comment