Sunday, August 30, 2015

ነዳጅ የያዘው መኪና ተቃጥሎ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ



zeway eth




በኢትዮጵያ ከ እለት ወደ እለት እየደረሰ ያለው የመኪና አደጋ አስፈሪና በተለይም በመኪና ረዥም መንገድ መሄድን የማያስመኝ እየሆነ መጥቷል:: ዛሬ ጠዋት ላይ በዝዋይ ከተማ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ ወደ እሳትነት ተቀይሯል::
ከአካባቢው ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ነዳጅ የያዘው የጭነት መኪና ከሕዝብ ንብረት ማመላለሻ አይሱዙ መኪና ጋር የተጋጩ ሲሆን ነዳጅ የያዘው መኪና እሳት ተነስቶበት ለሁለቱም መኪኖች መቃጠል ምክንያት ሆኗል:: እስካሁን የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት የመኪናዎቹ አስከርካሪዎች የሁኑ 2 ሰዎች ተቃጥለው ሕይወታቸው አልፏል:: ሆኖም ግን ፖሊስ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የሰጠው ነገር የለም::

No comments:

Post a Comment