Sunday, August 23, 2015

የደቡብ ሱዳን ግጭት መባባሱ ተዘገበ


የደቡብ ሱዳን ጦርነት በእስከአሁን ሂደት ከ 10 ሺህ በላይ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉና በመቶ ሺህዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስደት መንስኤ መሆኑ አይዘነጋም ይሁን እንጂ ለሀገሪቱ ሰላም ያመጣል ተብሎ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት የቅርብ ጊዜው የአዲስ አበባ ድርድር ውጤቱ የተጠበቀውን ያክል መሆን ሳይችል ቀርቷል
በሰላም ስምምነቱ ሰነድ ላይ ተቃዋሚው ሪክ ማቻር ፊርማቸውን ቢያኖሩም የሀገሪቱ መንግስት ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኪር ግን ጊዜ ይሰጠኝ በሚል ፊርማቸውን ሳያኖሩ ነው የተመለሱት ይህን ተከትሎ አሁን ላይ በሀገሪቱ ከባድ ጦርነት መቀስቀሱ ​​የተነገረ ሲሆን የሀገሬው ዜጎች እልቂት ከድጡ ወደማጡ እንዳይባባስ ከወዲሁ እየተሰጋ ይገኛልአቀፉ ማህበረሰብ የማእቀብ አለም ማስፈራሪያዎችን በተደጋጋሚ ለተፋላሚዎቹ ከመስጠት በዘለለ እስከአሁን ቁርጥ ያለ የመፍትሄ እርምጃ አልወሰደም ተብላል

No comments:

Post a Comment