Monday, January 25, 2016

ሕውሓት ይችን መልክዓ ምድር ከጎንደሬዎች ቀምቶ ወደትግራይ ለመጠቅለል እጅግ ዘርፈ ብዙ በደል በሰሜን ጎነደር ኗሪዎች ላይ ፈፅሟል።


ከሰሜን አውራጃ ተከዜን ተሻግሮ ፀለምትን እስከ አዳርቃይ የአርማደጋን ዋልድባን ጨምሮ በወረራ ይዞ ይገኛል በዛ የነበሩትን ታሪካዊ ነገሮች እያጠፋ የጎጥ ሥሞችን ሁሉ በትግርኛ አጠራር በመቀየር ላይ ሲሆን ።
በወገራ አውራጃ ላይ የወረረው መሬት ለትግራይ ክልል አንድ ዞን አስገኝቶላታል ።
የትግራይ መስተዳድር ይህን ከወገራ አውራጃ ሰዎችን አፈናቅሎ በያዘው ምድር ላይ ከመሀል ትግራይ የመጡ ሰዎችን ባንዴ ብቻ ከግማሽ ሚሊየን በላይ አስፍሮበታል የአርማጭሆን ድንግል ጫካ መዘጋ መንጥሮ የሽመል መብቀያ የነበረውን ወደምድረ በዳነት ቀይሮታል ይህ ምድር እጅግ መጠነ ሰፊ ነው ብዙ የወረዳ መስተዳድሮች ወጠውታል ፣የሰቲት ሁመራን ለምና ድንግል መሬት ለራሱ የትግራይ የግል ንብረት ሁኗል
ይህ የተግራይ ምዕራባዊ ዞን የቅፅል ሥሙም የልማት ኮሪደር ይሉታል ።
እነሱ የባለልማት ኮሪደር ሲፈልጉ የጎንደር ገበሬ የበሬ ግንባር የምታክል መሬት ተሰጥቶት በመኖርና ባለመኖር በድህነት እንዲማቅቅ ሲደረገ ።
ያችውንም ደጋፊ አይደለህም ተብሎ የመነጠቅ ዕድሉም ሰፊ ነው ።
መሬቱን ለጨካባቢው ሰው እንዳይጠቀምበት ተከልሎና ተከልክሎ ለኢንበስተር በሚል ውኃ እየጠጣ ቦዝኖ የሚኖር መሬትም አለ በቋራ በኩል የሚደረገው እንደዚህ ነው ።
ይህ በዚች ፅሁፌ ለመናገር የሞከርኩት የተጋነነ አይደለም በትክክል ራሱ ሕውሓት ማስተባበል የማይችልበት በደሉ ከጠቀስኩት በላይም የከፋና ተዘርዝሮ የማያልቅ ነው ።
በተለይ የጎንደርን ገበሬ በሱዳን ጠረፍ የሕውሓት ጦር ከሱዳን ጦር ጋር በመመሳጠር ለ25 ዓመት ብዙ በደል ተፈፅሟል ።
ከኘገበሬዎቹ ከአካባቢው ለቀው እንዲጠፉ አስቃቂ ግድያና ከነማሳቸው ሰዎች በእሳት እንዲጋዩ የተደረገበት አጋጣሚም በተደጋጋሚ የታየ ነው ።
ሱዳኖች በቀን እንደፈለጉ ማድረግ ሀብት
ከማውደም በላይ ዘረፋም ሲፈፅሙ የሕውሓት ጦር በትዝብት እንዲመመለከትና ። ይህን ግፍ ለመቋቋም የሚደራጁትን ገበሬዎች ጠንካራ ናቸው ተብለው በአካባቢው ሰዎች የሚታወቁትን ።የሕውሓት ጦር ሌሊት ሌሊት በየመኖሪያቸው እየታፈኑ ተወስደው የት እንደደረሱ ያልታወቁት አያሌ ናቨው አንታፈንም ያሉ በቤታቸው ሳሉ የተረሸኑትም ብዙ ናቸው ።
ባለፈው ዓመት እንደተፈፀመው ከሞት ያመለጠው የታች አርማጭሆው ነዋሪ ከመተማ ታፍኖ ወደሁመራ ተወስደው የራሳቸውን ቀብር እንዲቆፍሩ ከተደረገ በኋላ በተዓምር አምልጦ የሰጠው ምስክርነት በቂ መረጃ ነው ።

No comments:

Post a Comment