
የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፒሬ ነኩሩንዚዛ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ጦር ወደ አገራቸው የሚገባ ከሆነ እንደሚዋጉት ተናግረዋል ።
የፕሬዝዳንቱ ማስፈራሪያ የተደመጠው የአፍሪካ ህብረት ያለ ምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር መንግስት ፈቃድ 5000 ጦር ለመላክ መወሰኑን ማሳወቁን ተከትሎ ነው ።
ቢቢሲ በብሩንዲ ከሚያዚያ ወር ወዲህ 400 ሰው መገደሉንና 220.000 ሰዎች መፈናቀላቸውን ዘግቧል ። የአፍሪካ ህብረት ለዚህ ውሳኔ የበቃውም በዚህ መነሻነት እንደሆነ ይታመናል ።
ፕሬዘዳንቱ ባስተላለፉት ማስጠንቀቂያ የህብረቱ ጦር ያለ ፈቃዳቸው ድንበራቸውን ጥሶ የሚገባ ከሆነ እንዋጋዋለን ብለዋል።
“ሁሉም የብሩንዲን ድንበር ማክበር ይገባዋል ” ያሉት ነኩሩንዚዛ “የህብረቱ ጦር የሚገባ ከሆነም የምናየው ጥቃት እንደተፈፀመብን በመሆኑ ሁሉም ብሩንዲያዊ ይፋለማቸዋል” ብለዋል ።
በብሩንዲ ህገመንግስት መሰረት የውጪ ጦር ጣልቃ ሊገባ የሚችለው ጥያቄ ከአገር ውስጥ ሲቀርብ ወይም ህጋዊ መንግስት ስልጣን ላይ ከሌለ ብቻ ነው ማለታቸውን መንግስታዊው ራዲዮ አስደምጧል ።
ነኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር በፕሬዘዳንታዊው ወንበር ለመቀመጥ ማሳወቃቸው በአገሪቱ ሁከት ቀስቅሷል ።ባለሞያዎችም ሁከቱ ተባብሶ ወደ እርስበርስ ጦርነት ሊያመራ እንደሚችል ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል ።
ፕሬዘዳንቱ የተቃጣባቸውን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ባከሸፉ ሁለተኛ ወራቸው በሐምሌ ወር በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ የምርጫ ውድድር በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት ማሸነፋቸውን ቢያስታውቁም የፕሬዘዳንትነት ዘመናቸው መጠናቀቁን የሚነግሯቸውን ተቃዋሚዎቻቸውን ለማሳመን አልቻሉም ።
(ጦር ወደ ብሩንዲ ልከው ዶላር ለመሸቀል ያሰፈሰፉ የአፍሪካ መሪዎች ምን አይነት ምላሽ ይኖራቸዋል ብለው ይገምታሉ ?
የፕሬዝዳንቱ ማስፈራሪያ የተደመጠው የአፍሪካ ህብረት ያለ ምስራቅ አፍሪካዊቷ አገር መንግስት ፈቃድ 5000 ጦር ለመላክ መወሰኑን ማሳወቁን ተከትሎ ነው ።
ቢቢሲ በብሩንዲ ከሚያዚያ ወር ወዲህ 400 ሰው መገደሉንና 220.000 ሰዎች መፈናቀላቸውን ዘግቧል ። የአፍሪካ ህብረት ለዚህ ውሳኔ የበቃውም በዚህ መነሻነት እንደሆነ ይታመናል ።
ፕሬዘዳንቱ ባስተላለፉት ማስጠንቀቂያ የህብረቱ ጦር ያለ ፈቃዳቸው ድንበራቸውን ጥሶ የሚገባ ከሆነ እንዋጋዋለን ብለዋል።
“ሁሉም የብሩንዲን ድንበር ማክበር ይገባዋል ” ያሉት ነኩሩንዚዛ “የህብረቱ ጦር የሚገባ ከሆነም የምናየው ጥቃት እንደተፈፀመብን በመሆኑ ሁሉም ብሩንዲያዊ ይፋለማቸዋል” ብለዋል ።
በብሩንዲ ህገመንግስት መሰረት የውጪ ጦር ጣልቃ ሊገባ የሚችለው ጥያቄ ከአገር ውስጥ ሲቀርብ ወይም ህጋዊ መንግስት ስልጣን ላይ ከሌለ ብቻ ነው ማለታቸውን መንግስታዊው ራዲዮ አስደምጧል ።
ነኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር በፕሬዘዳንታዊው ወንበር ለመቀመጥ ማሳወቃቸው በአገሪቱ ሁከት ቀስቅሷል ።ባለሞያዎችም ሁከቱ ተባብሶ ወደ እርስበርስ ጦርነት ሊያመራ እንደሚችል ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል ።
ፕሬዘዳንቱ የተቃጣባቸውን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ባከሸፉ ሁለተኛ ወራቸው በሐምሌ ወር በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ የምርጫ ውድድር በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት ማሸነፋቸውን ቢያስታውቁም የፕሬዘዳንትነት ዘመናቸው መጠናቀቁን የሚነግሯቸውን ተቃዋሚዎቻቸውን ለማሳመን አልቻሉም ።
(ጦር ወደ ብሩንዲ ልከው ዶላር ለመሸቀል ያሰፈሰፉ የአፍሪካ መሪዎች ምን አይነት ምላሽ ይኖራቸዋል ብለው ይገምታሉ ?
No comments:
Post a Comment