Saturday, January 23, 2016

ሰበር ዜና ህወሀት ዳግም ለሁለት ተሰነጠቀ ተባለ።

የ”መቀሌው” እና የ”አዲስ አበባው” ህወሀት ተብለ ጠርዝ ለጠርዝ ሆነው እየተሻኮት ይገኛሉ። ብአዴን ከመቀሌው ህወሀት በኩል የመወገን አዝማሚያ እያሳየ ሲሆን ኦህዴድ እና አሻጉሊቱን ጠ\ሚ ጨምሮ ዴህዴን ከአዲስአበባ ህወሀት ጎን በማሽቃበጥ ላይ ይገኛሉ። አቦይ ስብሃት ሁለቱንም አክራሪ ህወሀቶች ለማስታረቅ እየጣሩ ነው። በትናንትናው እለት የመቀሌው ህወሀት መሪ የሆነውን የትግራይ ክልል መስተዳድር የሆነው አባይ ወልዱን አቦይ ስብሃት ደውለው ማስጠንቀቂያ እንደሰጡት ታማኝ ምንጮች ነግረውናል አቦይ ስብሃት ቃል በቃል በስልክ ለአባይ ወልዱ “አሁን በዚህ ጊዜ ነፍጠኞች (አማራ) እና ጠባቦች (ኦሮሞ) ተባብረው በጋራ እየሰሩ ከአለም መንግስታ ጫና እያስፈጠሩብን ባሉበት ወቅት የእርስ በርስ ውጊያች ውድቀታችንን ያፈጥነዋል” ብለውታል። በተመሳሳይ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥም ከፍተኛ ጫና መኖሩን እና ጦሩ አፈ ሙዙን ያዞርብናል የሚል ከፍተኛ ውጥረት መኖሩንም ምንጮቻችን አክልው ነግረውናል። በተያያዘ ዜና በኦሮሚያ የተነሳው የመብት ጥያቄ መቆጣጠር እንደተሳነው የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዥ ለበላይ አካላት “አንድ ሰው በገደልን ቁጥር ሌሎች ሺዎች አመፁንን እየተቀላቀሉ ነው። ወታደሩም ወገኖቻችንን አንገልም የሚል አዝማሚያ እያሳየ ነው” ብለው አሳውቀዋል። እንዲሁም በቅርቡ ለሱዳን ሊሰጥ በታሰበው መሬትን ተከትሎ በአማራ ክልል ይቀሰቀሳላ ተብሎ ሚጠበቀው ብረት የቀላቀለ ህዝባዊ ተቃውሞ በወያኔ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ፍረሀት መፍጠሩንም ማወቅ ችለናል።

No comments:

Post a Comment