
እማኝ ዘጋቢያችን የላኩልን መረጃ እንዲህ ይነበባል፡-
“በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ በፍኖተ ሰላም በሺንዲ ወረዳዎችና አካባቢዎች በበርበሬ ንግድ ላይ አዲስ አዋጅ አውጥተው ህዝቡን ለችግር ነጋዴውን ደግሞ ለኪሳራ እየዳረጉት ነው። አዲስ ያወጡት አዋጅ ለጎጃም ብቻ ሲሆን፡-
1ኛ. ሁሉም ነጋዴዎች በሚሸጡበት ቦታ ሁሉ ቅርንጫፍ እንዲኖራቸው ያስገድዳል። ለምሳሌ የቡሬ ነዋሪ የሆነ ነጋዴ መቀሌ መሸጥ ቢፈልግ ቅርንጫፍ ሊኖረው ግድ ነው፤ አዲስ አበባ ቢሆን ሌላ ተጨማሪ ቅርንጫፍ ሊኖረው ያስፈልጋል፤ ሽሬም ቢፈልግ እንዲሁ፤
2ኛ. ማንኛውም ነጋዴ ከነጋዴ ላይ መግዛት አይችልም፤ ለምሳሌ 90 ኩንታል መጫን የፈለገ 85 ኩንታል ኖሮት 5 ቢጎለው 5 ከነጋዴ ላይ ገዝቶ መሙላት አይችልም፤
3ኛ. ቫት እንዲጀምሩ ማለትም በቫት እንዲገዙ፤
4ኛ. ከ6 ወር በላይ መከዘን ወይም ማስቀመጥ አይቻልም።
ለምሳሌ 1 ኪሎ 60 ብር ቢገዛና በቀጣይ ጊዜ ቢቀንስ 50 ብር ቢሆን ከስሮም ቢሆን መሸጥ ግዴታው ነው።”
በማለት የአካባቢው ነጋዴና ሕዝብ እየተጋፈጠ ያለውን ችግር እንድናሰማላቸው ልከውልናል፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)
No comments:
Post a Comment