በኦሮሚያ እየተፈፀመ ያለውን ኢሰብአዊ ድርጊት ለመደበቅ እየሞከረ ያለው ህወሀት ኢህአዴግ ማክሰኞ እለት በዝግ በተካሄደው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ ላይ ሙክታር ከድርን በማንሳት አቶ በከር ሻሌ የክልሉ ፕሬዚዳንት እንዲሆን በህወሀቶች መወሰኑን ታማኝ መረጃዎች አረጋግጠዋል
አቶ በከር ሻሌ ከዚህ ቀደም የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ከመሆናቸው በፊት በሚኒስትር ዴኤታነት የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለወራት የሰሩ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ተነስተው ወደ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ተዛውረው እንዲሰሩ ተደርገው የነበሩት አቶ በከር፣ በጽሕፈት ቤቱ ለተወሰኑ ወራት በሚኒስትር ዴኤታነት ካገለገሉ በኋላ የአዳማ ከተማ ከንቲባ ሆነው መሾማቸውም የሚታወስ ነው፡፡
ከግንቦት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በሙስና ወንጀል በሕወሐት ተከሰው የታሰሩትን አቶ መላኩ ፈንታ ተክተው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የተደረጉ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በተመሣሣይ ሁኔታ የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ባላወቀበት ሁኔታ የክልሉ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በህወሀቶች የተወሰነ ሲሆን ምክር ቤቱም ከሰሞኑ ያፀድቀዋል ተብሎ ይታሰባል ከዚሁ ጋር በተያያዘ አቶ ሙክታር ከድር ወደሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር ተዛውረው እንደሚሰሩም የተገኘው መረጃ ያስረዳል። አቶ ሙክታር ከድር በጅማ እና ኢሉ አባቡራ አካባቢ ከፍተኛ ደጋፊ የነበራቸው ሲሆን በአንፃሩ አቶ በከር ሻሌ ኦቦ ገብረመድህን እስከመባል ያደረሰ ሥር የሰደደ የሕወሐት ተላላኪ መሆናቸውንም ለማወቅ ተችሏል።
አቶ በከር ሻሌ ከዚህ ቀደም የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ከመሆናቸው በፊት በሚኒስትር ዴኤታነት የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለወራት የሰሩ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ተነስተው ወደ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ተዛውረው እንዲሰሩ ተደርገው የነበሩት አቶ በከር፣ በጽሕፈት ቤቱ ለተወሰኑ ወራት በሚኒስትር ዴኤታነት ካገለገሉ በኋላ የአዳማ ከተማ ከንቲባ ሆነው መሾማቸውም የሚታወስ ነው፡፡
ከግንቦት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በሙስና ወንጀል በሕወሐት ተከሰው የታሰሩትን አቶ መላኩ ፈንታ ተክተው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የተደረጉ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በተመሣሣይ ሁኔታ የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ባላወቀበት ሁኔታ የክልሉ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በህወሀቶች የተወሰነ ሲሆን ምክር ቤቱም ከሰሞኑ ያፀድቀዋል ተብሎ ይታሰባል ከዚሁ ጋር በተያያዘ አቶ ሙክታር ከድር ወደሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር ተዛውረው እንደሚሰሩም የተገኘው መረጃ ያስረዳል። አቶ ሙክታር ከድር በጅማ እና ኢሉ አባቡራ አካባቢ ከፍተኛ ደጋፊ የነበራቸው ሲሆን በአንፃሩ አቶ በከር ሻሌ ኦቦ ገብረመድህን እስከመባል ያደረሰ ሥር የሰደደ የሕወሐት ተላላኪ መሆናቸውንም ለማወቅ ተችሏል።

No comments:
Post a Comment