Tuesday, February 23, 2016

ኦሮሚያ የጦርነት ቀጠና ሆናለች::ለሕዝብ ሰላማዊ ተቃውሞ ከባባድ የጦር መሳሪያዎች በክልሉ ሰፍረዋል::


በኢትዮጵያ የኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው የሕዝብ ጭቆና በቃኝ ንቅናቄ ዛሬ ከጠዋቱ ጀምሮ እስከ ምሽቱ ድረስ የቀጠለ ሲሆን ሕጻናት አዛውንት ወጣት ሳይለዩ የሚገድሉ እና የሚያፍሱ የአግኣዚ ሰው በላ ወታደሮች ጭፍጨፋቸውን ቀጥለዋል::ባልተተገበረ ሕገመንግስት ከለላነት አምባገነን ተግባራትን የሚፈጽመው የወያኔው ማፊያ ገዳይ አገዛዝ በርካታ ኢትዮጵያውያንን በመግደል እና በማቁሰል ላይ ይገኛል:: እምቢ ለነጻነቴ እምቢ ለመብቴ ያሉ የኦሮሞ ልጆች ትግላቸውን ከበፊቱ በበለጠ አጠናክረው ቀጥለዋል::
በደንቢ ዶሎ ለሰላማዊው ሕዝቡ የአይሮፕላን መጣያ ዙ23 የጦርነት ነጋሪት የሚጎስመው አገዛዝ በሕዝብ ላይ ጠምዶ እየተንቀሳቀሰ ሲገኝ በየአከባቢው እንዲሁ ከባድ መሳሪያዎችን የታጠቁ ወታደራዊ ካሚዮኖች ተሰማርተዋል::የመብቱን ጥያቄ ይዞ አደባባይ የወጣን ሕዝብ በጥይት መግደል ወንጀል መሆኑ ሲታወቅ ማንም ከተጠያቂነት እንደማያመልጥ የሕወሓት መሪዎች ሊያውቁ ይገባል::ተቃውሞ በዛሬው እለት ከወለጋ እስከ ሃረርጌ ጉጂ ከሸዋ እስክ ኢሊባቦር ተስፋፍቶ ቀጥሏል::ወያኔ እንደለመደው በሚዲያዎቹ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ እየነዛ የሚገኝ ሲሆን ታማኝነት ያሌላቸ እጅግ አሳፋሪ ሃሰቶችን በሕዝብ ላይ እየረጨ ይገኛል::
ድል ለጭቁን ሕዝቦች!!!

No comments:

Post a Comment