Monday, December 28, 2015

የዓርበኞች ግንቦት 7 ሠራዊት ያቀጣጠለው የነፃነት እሳት አሁንም በሰሜን ተራሮች እየጨሰ ነው፥


ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው፣
ጀግናው የዓርማጭሆ ልጅ ትግሉን ከጀግናው ሠራዊታችን በሲቃ እንደተረከበው የሚያሳዩ ድሎች በየመንደሩ እየተመዘገቡ ነው፥ የዓርማጭሆና የወልቃይት ጠገዴ ጀግና እስከ ትግራይ ድንበር እየተሻገረ በጠላት መንደር ስጋት መፍጠሩን ዓጠናክሮ ቀጥሏል፥
ባለፈው ዓርብ ለቅዳሜ ዓጥቢያ ሃምሌ 3፣ 2007 ዓ.ም ታች አርማጭሆ ጎደቤ ላይ ልዩ ኃይል እና ፀረ-ሽምቅ ጎራ ለይተው በመሰለፍ ግራ በተጋባ ሁኔታ እርስበርሳቸው በጥይት ተጠዛጥዘዋል፡፡ በሁለቱ የወያኔ ታጣቂዎች በተደረገው ለሰዓታት የዘለቀ ውግያ በትንሹ ስድስት አባላት ሲሞቱ በርከት ያሉ ቁስለኞች መሆናቸው ተገልጧል፡፡
ዘረኛውንና ፋሽስቱን የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ቡድን በጠመንጃ አምበርክኮ ሕዝብን የሥልጣን ባለቤት የማድረጉ የትጥቅ ትግል ከኤርትራ በርሃዎች አልፎ በኢትዮጵያ መሬት ላይ በአስተማማኝ ሁኔታ እግሩን በመትከሉ፥ ህወሓት ወያኔ ከአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ብቻ ሳይሆን ከወልቃይትና ከአርማጭሆ ህዝብ በእያቅጣጫው የተከፈተበትን ፋታ የሌለውና ጠንከር ያለ የተኩስ ናዳ ፈፅሞ መቋቋም አልቻለም፡፡

No comments:

Post a Comment