
የህወሓት አገዛዝ በጅንካ የተነሳውን ጠንካራ ህዝባዊ እምቢተኝነት ለማርገብ ከሌላ አካባቢ የፌደራል ፖሊስና ልዮ ኃይል ጦር ጭኖ በአካባቢው አስፍሯል፡፡ ሆኖም አመፁን በኃይል ለማብረድ በአካባቢው ለሚገኙ የህወሓት የታጠቁ ኃይሎች ህዝቡ በአንድነት ተባብሮ ምግብና ውሃ መሸጥ በማቆሙ የፌደራል ፖሊስና የልዩ ኃይል አባላት በአካባቢው ለመቆየት በእጅጉ ተቸግረው ይገኛሉ፡፡
አገዛዙ ከሌላ አካባቢ ምግብና ውሃ ገዝቶ በማቅረብ ችግሩን በማቃለል የታጠቁ ኃይሎቹን በአካባቢው ለማቆየት ጥረት እያደረገ ነው፡፡
አገዛዙ ከሌላ አካባቢ ምግብና ውሃ ገዝቶ በማቅረብ ችግሩን በማቃለል የታጠቁ ኃይሎቹን በአካባቢው ለማቆየት ጥረት እያደረገ ነው፡፡
በኮንሶ፣ ቦረና፣ ተልተሌ፣ በና፣ ፀማይ፣ እና ሐመር ከፍተኛ ረሃብ መግባቱ ተሰማ፡፡
በበርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ምክንያት ከ16 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ለምግብ እጥረት ተዳርጎ የሚደርስለት ጠፍቶ በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ከፍተኛ እልቂት እያንዣበበበት ይገኛል፡፡ ነገር ግን የህወሓት አገዛዝ አሁንም ቢሆን የስልጣን ዕድሜውን ማራዘም ለሚያስችሉት ተግባራት ከፍተኛ ወጭ እያፈሰሰ በረሃብ የሚያልቀው ኢትዮጵያዊ ምንም ደንታ አልሰጠውም፤ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመድፋት ከፍተኛ ድግስ ማሰናዳቱን እና በከፍተኛ የውሎ አበል ክፍያ በያዳራሹ በስብሰባ ስም መመሸሸጉን አሁንም ቀጥሎበታል፡፡
ህወሓት ድርቅንና በህዝብ ላይ የሚመጣን የረሃብ እልቂት እንዳውም ለገቢ ምንጭነት የመጠቀም የቆየ ልምድ እና ባህል እንዳለው ብዙዎቹ በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡
በተለይም ደግሞ አሁን በኮንሶ፣ ቦረና፣ ተልተሌ፣ በና፣ ፀማይ፣ እና ሐመር የገባው አደገኛ ጠኔ ከሌሎች አካባቢዎች የከፋ እና ጊዜ የማይሰጥ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
በበርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ምክንያት ከ16 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ለምግብ እጥረት ተዳርጎ የሚደርስለት ጠፍቶ በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ከፍተኛ እልቂት እያንዣበበበት ይገኛል፡፡ ነገር ግን የህወሓት አገዛዝ አሁንም ቢሆን የስልጣን ዕድሜውን ማራዘም ለሚያስችሉት ተግባራት ከፍተኛ ወጭ እያፈሰሰ በረሃብ የሚያልቀው ኢትዮጵያዊ ምንም ደንታ አልሰጠውም፤ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመድፋት ከፍተኛ ድግስ ማሰናዳቱን እና በከፍተኛ የውሎ አበል ክፍያ በያዳራሹ በስብሰባ ስም መመሸሸጉን አሁንም ቀጥሎበታል፡፡
ህወሓት ድርቅንና በህዝብ ላይ የሚመጣን የረሃብ እልቂት እንዳውም ለገቢ ምንጭነት የመጠቀም የቆየ ልምድ እና ባህል እንዳለው ብዙዎቹ በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡
በተለይም ደግሞ አሁን በኮንሶ፣ ቦረና፣ ተልተሌ፣ በና፣ ፀማይ፣ እና ሐመር የገባው አደገኛ ጠኔ ከሌሎች አካባቢዎች የከፋ እና ጊዜ የማይሰጥ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
No comments:
Post a Comment