
ወያኔ /ህወኃት የአማራን ህዝብ በጠላትነት ፈርጆ ከተነሳበት ከ1967 ዓ• ም ጀምሮ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚቆረቆሩ ወገኖችነ እየታደኑ ተገድለዋል፣ በመገደልም ላይ ይገኛሉ።
ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ ወያኔ በሎሌው ብአዴን አማካኝነት የአማራን ህዝብ ማሰር፣ ማፈናቀልና መግደል አጠናክሮ ቀጥሎበታል። በአሁኑ ሰዓት በወልቃይት ፀገዴ የአማራ ህዝብ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለው አሰቃቂ ስቃይ ታሪክ ይቅር የማይለው በደል ነው። በአማራ ህዝብ ስቃይ፣ ስደት፣ መከራ፣ መፈናቀልና ሞት ምክንያት የሆነውን ህዳር 11 ቀን የወያኔን የድል በዓል ለማክበር ከበሮ እየደለቀ ያለውን ብአዴንን በቃ ብሎ ህዝባችን ለነፃነቱ መነሳት አለበት።
ስለዚህ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የምትኖሩ የአማራ ተወላጆች በአስቸኳይ በመሰባሰብ ለዚህ አረመኔያዊ ግፍ የሚመጥን ቁመና በመፍጠር ህዝባችንን ከመፈናቀል፣ ከስደትና ከሞት ለመታደግ በእውነት የአማራን ህዝብ የሚወክል ድርጅት መመስረት ይጠበቅብናል። ይህን ግፍ እያየን እንዳላዬን፣ እየሰማን እንዳልሰማን ዝም ብንል መዳን ለአማራ ህዝብ ከሌላ ስፍራ ይመጣለታል። እኛ ግን በታሪክ መታሰቢያ አይኖረንም። በመሆኑም መላው የአማራ ተወላጅ ገበሬው፣ ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ምሁሩና ወታደሩ በአስቸኳይ በያለበት በመደራጀት የትውልድ አድን ንቅናቄ እንዲጀምር እናሳስባለን።
እኔ እንደ አማራ ተወላጅነቴና እንደ ኢተረዮጵያዊነቴ በዚህ ችግር ዙሪያ ከተለያዩ የአማራ ምሁራን ጋር ውይይት በማድረግ ላይ እገኛለሁ። በቅርብ ቀን ይህን የህዝብ ስቃይና ሞት የሚመክት እውነተኛ የአማራ ንቅናቄም እንፈጥራለን። እስከዚያው ግን ህዝባችን የብአዴንንና የወያኔን እኩይ ተግባር በያለበት በመመከት በቅርብ ለሚመሰረተው ንቅናቄ ግብአት የሚሆን አቅም እንዲፈጥር በአክብሮት እንጠይቃለን።
ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ ወያኔ በሎሌው ብአዴን አማካኝነት የአማራን ህዝብ ማሰር፣ ማፈናቀልና መግደል አጠናክሮ ቀጥሎበታል። በአሁኑ ሰዓት በወልቃይት ፀገዴ የአማራ ህዝብ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለው አሰቃቂ ስቃይ ታሪክ ይቅር የማይለው በደል ነው። በአማራ ህዝብ ስቃይ፣ ስደት፣ መከራ፣ መፈናቀልና ሞት ምክንያት የሆነውን ህዳር 11 ቀን የወያኔን የድል በዓል ለማክበር ከበሮ እየደለቀ ያለውን ብአዴንን በቃ ብሎ ህዝባችን ለነፃነቱ መነሳት አለበት።
ስለዚህ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የምትኖሩ የአማራ ተወላጆች በአስቸኳይ በመሰባሰብ ለዚህ አረመኔያዊ ግፍ የሚመጥን ቁመና በመፍጠር ህዝባችንን ከመፈናቀል፣ ከስደትና ከሞት ለመታደግ በእውነት የአማራን ህዝብ የሚወክል ድርጅት መመስረት ይጠበቅብናል። ይህን ግፍ እያየን እንዳላዬን፣ እየሰማን እንዳልሰማን ዝም ብንል መዳን ለአማራ ህዝብ ከሌላ ስፍራ ይመጣለታል። እኛ ግን በታሪክ መታሰቢያ አይኖረንም። በመሆኑም መላው የአማራ ተወላጅ ገበሬው፣ ተማሪው፣ ነጋዴው፣ ምሁሩና ወታደሩ በአስቸኳይ በያለበት በመደራጀት የትውልድ አድን ንቅናቄ እንዲጀምር እናሳስባለን።
እኔ እንደ አማራ ተወላጅነቴና እንደ ኢተረዮጵያዊነቴ በዚህ ችግር ዙሪያ ከተለያዩ የአማራ ምሁራን ጋር ውይይት በማድረግ ላይ እገኛለሁ። በቅርብ ቀን ይህን የህዝብ ስቃይና ሞት የሚመክት እውነተኛ የአማራ ንቅናቄም እንፈጥራለን። እስከዚያው ግን ህዝባችን የብአዴንንና የወያኔን እኩይ ተግባር በያለበት በመመከት በቅርብ ለሚመሰረተው ንቅናቄ ግብአት የሚሆን አቅም እንዲፈጥር በአክብሮት እንጠይቃለን።
ሁለንተናዊ ነፃነትና ክብር ለአማራ ህዝብ!!
ነፃነት ለሃበሻ
No comments:
Post a Comment