አካባቢያችንን በብሄር ለማተራመስ በደቡብ ወገኖቻችን ስም የሚነግዱ ግለሰቦች ኦሮሞና አማራን ለማጋጨት የተጀመረው ዘመቻ ከወዲሁ ገድብ ሊበጅለት ይገባል። በተለይ ደቡብን እንወክላለን የሚሉ ግን የራሳቸውን ድብቅ አጀንዳ ለማስፈፀም የሚራወጡ ግለሰቦች ሰሞኑን ለህዝብ አሳቢ ለሃገር ተቆራቋሪ መስለው ዲፕሎማት ሲራክ ላይ የከፈቱት ዘምቻ በኦሮሞ ህዝብ የተፈፀመ እንዳልሆነ እይታወቀ ለምን ብሄራችንን የዚህ አስፀያፊ የስም ማጥፋት ዘመቻቸው አካል ለማድረግ እንደፈለጉ ግልጽ አይደለም። በየትኛውም አቅጣጫ የኦሮሞን ህዝብ የሁከት መነሻ ለማድረግ ለምን ተፈለገ ? ይህ በነሰመረ እና ሙሉካ የሱፍ የተጀመረው አሰቃቂ ዘምቻ ማንን ለመምታት ነው ? ቆንስላው የሁሉንም ብሄር ተዋጾ ግበአት ያደረገ በመሆኑ በቆንሳው ዙሪያ ለሚከሰቱት ማናቸውም ችግሮች ሚሲዮኑ መጠየቅ ሲገባው አቶ ሲራክን ለምን ነጥሎ ማጥላላት ማብጠልጠል አሰፈለገ ? አቶ ሲራክ ላይ ዘምቻ በተከፍተ ማግስት ከጉዳዩ ጋር በምንም ማመዘኛ ግንኙነት ከሌለው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ጋር ማያያዝስ ለምን ተፈለገ ? እነስመረ የአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠር ዘምቻ ለምን በኦሮሞ ህዝብ ስም ማካሄድን መረጡ ? የሚሉ ጥያቄዎችን ወደፊት በዝርዝር ለማየት የሚሞከር መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ዛሬ በፍቅር በሰላም እየኖረ ያለውን ማህበረሰብ በብሄር ለማተራመስ ነዚህ ወገኖች የጀመሩት ዘምቻ ከቆንስላ አልፎ በአካባቢያችን የሚገኙ ታዋቂ የአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ ያነጣጠረው ጣላቻ የነሰመረን የነሙልካ ድብቅ አጀንዳ እንጂ የኦሮሞ ህዝብ እንዳለሆነ የበለጠ ግልጽ ማድረግ እንወዳለን ፡፡ እነዚህ በደቡብ ህዝብ ስም ቆንሳላ ውስጥ መሽገው የአዞ እንባ የሚያነቡ ግለሰቦች እና አጋሮቻቸው አአካባቢያችንን በብሄር ለማተራመስ እያሰሙ ያለው ጩሀት ገድብ ሊበጅለት ይገባል። ቆንስል ሙንታሀ የጉዳዩን አሳስቢነት ግንዛቤ ውስጥ አስገብተው አብረው እየበሉ አብረው እየጠጡ እነሰመረ የስራ በልደረባዎ ላይ የጀመሩትን የስም ማጥፋት ዘምቻ ማስቆም ይጠበቅቦታል። ከሁሉም በላይ በህዝባችን ስም «፡ኦሮሞ » እይነገዱ የሚገኙ እነዚህ ግለስቦች ድብቅ አጀንዳዎቻውን በዚህ መልኩ ለማስፈፀም መሞከራቸው ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚከፋ ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ ጊዜ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆን የለበተም ። የአቶ ሲራክ ለግምገማ መቅረብ አለመቅረብ በካባቢያችን የብሄር ግጭት ማስነሳት በሚችል መልኩ ቅስቀሳ ማድረግ በስደት ዓለም ለሚኖረው ህዝባችን በእንቅርት ላይ ጆር ደግፍ ስለሚሆን ሊታሰብበት ይገባል። አቶ ሲራክ መጠየቅ በሚገባው ይጠየቅ እንጂ በአማራነቱ አሊያም የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ በመሆኑ ብቻ ሊገፋ እና አመታት ሲሰራ የነበር ድንቅ ስራዎቹ በግለሰብ ጥላች በአንድ ቀን ጀምበ ሊናድ አይገባም ።ማንም ምንም ይሁን ምን ሊጠየቅ በሚገባበት ነገር ሁሉ መጠየቅ እንዳለበት ግልጽ ቢሆነም ቆንስላው እንደ ተቋም በደንብና ስረአት የሚመራ ሆኖ ሳለ በነ ቆንስላ ሙንተሃ አስተባባሪነት አቶ ሰመረ እና የዘንድሮ የሴቶች ማህበር ተብየ ሊቀመንበር ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ አንድ ብሄር ላይ ለመዝመት በእጅ አዙር እየተፈፀመ ያለው አስፀያፊ ና አስነዋሪ የስም ማጥፋት ዘምቻ በተለይ ወ/ሮ ሙንተሃ ካሉበት የስራ ኃላፊነት አንጻር የሚመጥን ባለመሆኑ ሊታሰብበት ይገባል። ቆንስላውን በብሄር ለማመስ በኦሮሞ ህዝብ ሽፋን አንዳንድ ደቡብን ወክለናል በሚሉ ግለሰቦች በየሶሻል ሚዲያ ገጽ ላይ የሚለጠፈው ፈር የለቀቀ አካሄድ ለአካባቢያችን ሰላም ጠንቅ መሆኑ ልብ ሊባል ይገበዋል። አያበሬ ምነው ገደሉን ሳታይ አየነት ግልጽ ሰህተት ውስጥ በመግባት በአካባቢያችን ታዋቂ ሰዎችና በቆንስላ ሃላፊዎች ላይ የተጀመረው የስም ማጥፋት ዘመቻ ሽፋን መስጫው መልካም አስተዳደር የሁን እንጂ ግቡ በአካባቢያችን የአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ ያነጣጠር ነው ። ቆንሳል ግቢ ውስጥ እየተፈፀመ ካለው ፈር የለቀቀ ድርጅታዊ አሰራር ሃሜትና ግምገማ እየታየ ያለው አስነዋሪ ተግባር አደባባይ ወጥቶ አንዱ በሌላው ላይ እያስወራ ያለው አስነዋሪ ድርጊት በአንድ ብሄር ላይ ያነጣጠር የስም ማጥፋት ዘምቻ በመሆኑ ከወዲሁ ሊገደብ ይገበዋል ። ህይወት ፀጋዬ ከጅዳ ቆንስላ ግቢ

No comments:
Post a Comment