
ግብጽና ኢትዮጵያ ሊዋጉ ነው እንዴ? ይሄ መግለጫ አላማረኝም
“በሰላም የመኖር ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ግብጽ የተለያየ መስርያ ስለገዛች በመሳርያ ኃይል ኢትዮጵያን አታንበረክክም:: ነው እንጂ ግብጽን አንፈራም:: ግብጽ ጠቅላላ አገር ምድሩን መሳርያ ማድረግ ትችላለች ከፈለገች:: የሚዋጋው ግን መሳርያ አይደለም:: እኛም ራሳችንን የመከላከል መብት አለን:: እንከላከላለንም” ኃይለማርያም ደሳለኝ
“ግብጽ ከካይሮ ተነስታ ኢትዮጵያን አታጠቃም:: እኩይ ዓላማ ያላቸው ጎረቤቶቻችን ለዚህ አላማ ድጋፍ ከሰጡ ግን እናስጠነቅቃለን:: ጣታቸውን ካንቀሳቀሱ አስቀድመን እንጨርሳቸዋለን” ኃይለማርያም ደሳለኝ
“ግብጽ ከካይሮ ተነስታ ኢትዮጵያን አታጠቃም:: እኩይ ዓላማ ያላቸው ጎረቤቶቻችን ለዚህ አላማ ድጋፍ ከሰጡ ግን እናስጠነቅቃለን:: ጣታቸውን ካንቀሳቀሱ አስቀድመን እንጨርሳቸዋለን” ኃይለማርያም ደሳለኝ
ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲህ አይነት መራር መግለጫ ሲሰጡ ብዙም አይሰሙም:: ዛሬ ግን ግብጽንም ለግብጽ ድጋፍ ሊያደርጉ የሚችሉ የኢትዮጵያን ጎረቤቶች መራር ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል::
“አስቀድመን እንጨርሳቸዋለን” እስከማለት የደረሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩም ግብጽንም አልማሯትም:: ” ግብጽ አገር ምድሩን መሳርያ ብታደርገው መሳርያ ብቻውን አይዋጋም” እስከማለት ያደረሳቸው ምን ይሆን?
“አስቀድመን እንጨርሳቸዋለን” እስከማለት የደረሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩም ግብጽንም አልማሯትም:: ” ግብጽ አገር ምድሩን መሳርያ ብታደርገው መሳርያ ብቻውን አይዋጋም” እስከማለት ያደረሳቸው ምን ይሆን?
የኢትዮጵያ ደህንነት መስሪያ ቤት ዋና ሰው የሆኑትን አቶ ጌታቸው አሰፋም ያለወትሯቸው እዚህ አሜሪካ መሆናቸው ተወስቷል::ኢሳትንም ከራሺያ ሳተላይት ለማውረድ ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ ዘመቻ እንዳካሄደች ኢሳት ዘግቧል:: በተመሳሳይ ዜናም ኢትዮጵያ ሰራዊት ምልመላ መጀመሯ ተዘግቧል::
ስምንትና ዘጠኝ ሚሊዮን ሰው በረሃብ ውስጥ ባለበት ሰዓት የወቅቱ ዜና ረሀቡና እርዳታ መሆን ሲገባው ይሄን ጦርነት መሰል መግለጫ በዚህ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒትሩ የሰጡት ምን ችግር ቢኖር ይሆን?
No comments:
Post a Comment