Monday, April 18, 2016

የአርማጭሆ ሕዝብ ለብአዴን ማስጠንቀቂያ ሰጠ

በመላው አርማጭሆ የሚኖረው ህዝብ ብአዴን አመራር ውስጥ አማራ መስለው ገብተው ህዝቡን በዘር የሚያጋጩ፣ ታጋዮችን እየጠቆሙ የሚያስይዙ፣ እንዲሁም ኢትዮጵያን ለም መሬት ለሱዳን ለማስረከብ በስወር የሚሰሩ፣ የወያኔሰላዎች እየበዙ መምጣታቸውን እያወቀ ብአዴን ምንም እርምጃ ሊወስድ ማለመቻሉ ህዝቡ ተቆትቷል። በዚህም ምክንያት፣ ህዝቡ በቁጣ ለብአዴን መሪዎች ከወያኔ አሽከርነት ነጻ እንዲወጡ ጠይቋል። በተጨማሪ ማንኛውም የብአዴን ባለስልጣን ፣ የጎንደር ደንበር ተከዜ መሆኑን የማይቀበል ከሆነ እንዲሁም፣ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን መሰጠቱን የማይቃወም ከሆነ ጠላታችን መሆኑን ታወቆ ከአባቢው እንዲነሳልን ብለው ጠይቀዋል።
በመጨረሻም፣ ብአዴን ለራሱ ቢል ከህዝቡ ጎን ይሰለፍ ካልሆነ ግን “ያለ ብአዴን ሀገራችንን እናስከብራለን፣ ድሮም አርማጭሆ ራሱን ይችላል ተብሎ ተቀኝቶለታል” በማለት ምክርና ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

No comments:

Post a Comment