Monday, April 18, 2016

ባልታወቀ ምክንያት ሁለት ጥንዶች ከያዙበት አልጋ ሞተው ተገኙ


ዛሬ ደግሞ 09.08.2008
ባልታወቀ ምክንያት ሁለት ጥንዶች ከያዙበት አልጋ ሞተው ተገኙ
የሞቱትን ጥንዶች ለምርመራ ይዘው የሄዱት ቤተሰቦቻቸውና አብረው የሄዱት ሰወች ጋር ከመቀሌ ሲመለሱ ቆቦ ከተማ
ሲደርሱ የተሳፈሩበት ሚኒባስ ከተሳቢመኪና ጋ በመጋጨቱ በአደጋው ግማሾቹ ለሞት ተዳርገዋል።
ነፍስ ይማር።
ሞትን ሞት
ባኮረፈ ሰማይ በጋ በዋለበት
በተረገመ አፈር ሀፅያት በበዛበት
ጭጭ ባለው ባህር ውሃ ጥም ተድሶ
የማያቋርጥ ሞት ሂዶ ሂዶ ፈሶ
የዝምታ ኩሬ ምንጩ ደፈረሰ
ልክ እንደታቻምና ዛሬም ተለቀሰ
ቢጨለፍ እማያልቅ ሀዘን ተወረሰ
በፍቅር ተቃቅፈው እስከዚያ ሲያሸልቡ
የሞት ፅዋ ቀምሰው አልቃሽን ሲራቡ
ሞትን ሞት ሊቀብር ተከታይ አዘለች
ሀገሬም አኩርፋ በሞት ቂም ይዛለች
ሞታችሁ ሁላችንንም አሳዝኖናል ።ለመላ ቤተሰብ መፅናናትን
እመኛለሁ።
መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.

No comments:

Post a Comment