Sunday, April 17, 2016

የደቡብ ሱዳን ታጣቂ ሃይሎች በኢትዮጵያ ጉዳት አደረሱ

ከደቡብ ሱዳን የተነሱ ሀይሎች ባደረሱት ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን መገደላቸው ተዘገበ፡፡ ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱ ናቸው የተባሉቱና ከሙርሌ ጎሳ እንደሆኑ የተገመቱት እነዚህ የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግረው ጥቃት የፈጸሙት ሀይሎች በኢትዮጵያ ባሉ የኑዌር ጎሳዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሳቸውንና ቁጥራቸው እስከ 170 የሚደርሱትን ሳይገድሉ እንዳልቀረ ተዘግቧል፡፡ ጥቃቱ በደረሰበት ጋምቤላ ህይወታቸው የተረፈ ሰዎች እንደተናገሩት ከሆነ ከደቡብ ሱዳን የተነሱቱ ሀይሎች በጄኮውና በኒያንያንግ ወረዳዎች አስር መንደሮች ላይ ድንገተኛ ጥቃት መክፈታቸውን፤ ካጠፉት የሰው ህይወት በተጨማሪም በቤት እንስሳትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡……

No comments:

Post a Comment