Wednesday, April 27, 2016

ቅዳሜና ዕሁድ በጋምቤላ ከተማ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከተካሄደ በኋላ መንግስት መጠነ ሰፊ የአፈሳ እርምጃ እየወሰደ ነው።


ቅዳሜና ዕሁድ በጋምቤላ ከተማ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከተካሄደ በኋላ መንግስት መጠነ ሰፊ የአፈሳ እርምጃ እየወሰደ ነው። ዛሬ ጋምቤላ ከተማ ቤት ለቤት አሰሳ ሲደረግ ነው የዋለው። ሆቴሎች መደብሮች ተበርብረዋል። በከተማዋ የሰው እንቅስቃሴ ገደብ ተጥሎበታል። በየመንገዱ መታወቂያ የሚጠይቁ ፌደራል ፖሊሶች ነዋሪውን ሲያንገላቱት፡ ወጣት ከሆነ ሲደበድቡት እንደነበረ እማኞች ገልጸዋል። ”በኦሮሚያ ተቃውሞ ያልተሳካላቸው ጸጉረ ልውጦች ገብተዋል” በሚል ፍተሻው ከፍተኛ እንደነበረ ያነጋገርናቸው አስታውቀዋል። ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን በጋምቤላ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ ማስጣል ያልቻለ ፌደራል ፖሊስ፡ ገዳዮቹ ላይ አንድም እርምጃ ሲወስድ ያልታየ መንግስት፡ በሟች ወገኖች ላይ ጡንቻው ፈርጥሞ ታየ – ጋምቤላ ላይ።

No comments:

Post a Comment