
በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ትምህርት ቤቶች የክርስቲያንነት መታወቂያችንን ማዕተብ ማሰር እንደሚከለከል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ሺፈራው አስታወቁ!
የመንግሥትን የሴኩላሪዝም መርሖና የፀረ አክራሪነት አጀንዳ ተገን
በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ርእዮታዊ
እና ሃይማኖታዊ ጥላቻቸውን በማስተጋባት የሚታወቁት ሚኒስትር
ሺፈራው፣ ይህን መናገራቸው የተጠቆመው፣ ከነሐሴ 18ቀን 2006 ዓ.ም.
ጀምሮ እስከ መስከረም 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ በዘለቀውና በኹለት ዙሮች በተካሔደው የመንግሥት መካከለኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ ነው፡፡
በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ርእዮታዊ
እና ሃይማኖታዊ ጥላቻቸውን በማስተጋባት የሚታወቁት ሚኒስትር
ሺፈራው፣ ይህን መናገራቸው የተጠቆመው፣ ከነሐሴ 18ቀን 2006 ዓ.ም.
ጀምሮ እስከ መስከረም 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ በዘለቀውና በኹለት ዙሮች በተካሔደው የመንግሥት መካከለኛ አመራሮች ሥልጠና ላይ ነው፡፡
በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ በተካሔደውና 800 ያህል መካከለኛ አመራሮች
በተሳተፉበት የፖሊሲና ስትራተጂ ሥልጠና ‹‹የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ
መንግሥት ግንባታና ፈተናዎቹ›› የሚለውን ሰነድ የሚያብራራና በፓወር
ፖይንት የተደገፈ ጽሑፍ ያቀረቡት ሚኒስትሩ የመንግሥትን የሴኩላሪዝም መርሖ መነሻ ያደረገ ነው የተባለ ጥያቄ ከአንዲት ተሳታፊ ቀርቦላቸዋል፡፡
እንደ ስብሰባው ምንጮች፣ የተሳታፊዋ ጥያቄ፣ ‹‹በቢሮ ፊታቸውን
ተሸፍነው የሚመጡ ሙስሊሞችን አለባበሳቸው ከቦታው አንፃር ያለውን ተገቢነት በማንሣት እንዲያወልቁ ስንጠይቃቸው ‘እኛ ይኼን የምናወልቅ ከኾነ ኦርቶዶክሱም ክሩን ይበጥስ’ ይሉናል፤ ይኼን እንዴት ነው የምንታገለው?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹መንግሥታችን ሴኩላር ነው›› ሲሉ በጠያቂዋ የተጠቀሰውን ዐይነት
አለባበስ የተቹት ሚኒስትሩ፣ ‹‹ማተቡም ቢኾን የጊዜ ጉዳይ
ነው፤ እንደ የሃይማኖት መለያ እስካገለገለ ድረስ አደረጃጀታችንን ስንጨርስ ማተብም ቢኾን መውለቁ አይቀርም፤›› የሚል ምላሽ መስጠታቸው ተገልጧል፡፡
በተሳተፉበት የፖሊሲና ስትራተጂ ሥልጠና ‹‹የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ
መንግሥት ግንባታና ፈተናዎቹ›› የሚለውን ሰነድ የሚያብራራና በፓወር
ፖይንት የተደገፈ ጽሑፍ ያቀረቡት ሚኒስትሩ የመንግሥትን የሴኩላሪዝም መርሖ መነሻ ያደረገ ነው የተባለ ጥያቄ ከአንዲት ተሳታፊ ቀርቦላቸዋል፡፡
እንደ ስብሰባው ምንጮች፣ የተሳታፊዋ ጥያቄ፣ ‹‹በቢሮ ፊታቸውን
ተሸፍነው የሚመጡ ሙስሊሞችን አለባበሳቸው ከቦታው አንፃር ያለውን ተገቢነት በማንሣት እንዲያወልቁ ስንጠይቃቸው ‘እኛ ይኼን የምናወልቅ ከኾነ ኦርቶዶክሱም ክሩን ይበጥስ’ ይሉናል፤ ይኼን እንዴት ነው የምንታገለው?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹መንግሥታችን ሴኩላር ነው›› ሲሉ በጠያቂዋ የተጠቀሰውን ዐይነት
አለባበስ የተቹት ሚኒስትሩ፣ ‹‹ማተቡም ቢኾን የጊዜ ጉዳይ
ነው፤ እንደ የሃይማኖት መለያ እስካገለገለ ድረስ አደረጃጀታችንን ስንጨርስ ማተብም ቢኾን መውለቁ አይቀርም፤›› የሚል ምላሽ መስጠታቸው ተገልጧል፡፡
ማዕተብ÷ የሲኦል መሠረት የተናወጠበት፣ ሰውንና እግዚአብሔርን ለዘመናት ለያይቷቸው የነበረው የጠብ ግድግዳ የተናደበት፣ የሞት ኃይሉ ተሽሮ የትንሣኤ መንገድ የተከፈተበት መስቀል ትእምርት በመኾኑ በተሳሳተ የሴኩላሪዝም ግንዛቤ ‹‹ማዕተቡም ሊወልቅ ይችላል›› ማለት፣ ‹‹ሃይማኖትን ከማስካድና እንደ ሰቃልያነ አምላክ አይሁድ መስቀሉን ለመቅበር ከመሞከር ተለይቶ አይታይም፤ ጉዳዩንም ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንና ታሪካዊ ትውፊት እንደማፋለስ የሚታይ ነው!
ሁላችንም ምዕመናን ማዕተባችንን ጠበቅ በማድረግ ለእምነታችንን ያለንን ፍቅር እስከ መስዋዕትነት የምንገልጽበት ጊዜ ቀርቧል!
ማተብሽን ፍች በጥሽው ቢሉኝ
እኔስ ከነ አንገቴ ውሰዱት አልኩኝ
እኔስ ከነ አንገቴ ውሰዱት አልኩኝ
ፊተኛ ነንና አንዳንሆን ኋላኛ
ህዝቤ ተነቃቃ ተነስ አትተኛ
ጅብ ከሄደ ውሻ እንዳይሆን ጩኽቱ
የተዋህዶ ልጆች አሁነ ነው ሰዓቱ
አይተን እንዳላየን ስንቱን አሳልፈናል
የእርሱ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም ብለናል
አሁን ግን ይበቃል ዝምታው ይሰበር
ይገለጥ ይታወጅ የተዋህዶ ሚስጢር
ተዋህዶ ሀይማኖቴ
የጥንት ነሽ የአናትና አባቴ
ማህተቤን አለበጥስም
ትኖራለች ለዘላለም!
ህዝቤ ተነቃቃ ተነስ አትተኛ
ጅብ ከሄደ ውሻ እንዳይሆን ጩኽቱ
የተዋህዶ ልጆች አሁነ ነው ሰዓቱ
አይተን እንዳላየን ስንቱን አሳልፈናል
የእርሱ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም ብለናል
አሁን ግን ይበቃል ዝምታው ይሰበር
ይገለጥ ይታወጅ የተዋህዶ ሚስጢር
ተዋህዶ ሀይማኖቴ
የጥንት ነሽ የአናትና አባቴ
ማህተቤን አለበጥስም
ትኖራለች ለዘላለም!
ሼር በማድረግ ለሁለም ሰው መረጃውን እናድርስ!!
No comments:
Post a Comment