Tuesday, September 15, 2015

ሰሜን ጎንደር ዞን የሚኖሩ አስተዳዳሪዎችና የህዝብ ተወካዮች መሬትን በተመለከተ ስብሰባ ማካሄዳቸው ታወቀ።

በሰሜን ጎንደር ዞን ወረዳዎች መተማ ሳንጃና ጭልጋ የሚገኙ አስተዳዳሪዎች የሚሊሻ ኮማንደሮችና ከ40 በላይ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች በተገኙበት ነሓሴ 24 / 2007 ዓ/ም ስብሰባ ማካሄዳቸውን የገለፀው ሪፖርቱ የስብሰባው ዋና አጀንዳም ከኢህኣዴግ የምናገኘው ለውጥ የለም፤ መሬታችን ራሳችንን ማስተዳደር አለብን? መሬታችን አሳልፈን አንሰጥም? የሚሉና ሌሎችን እንደነበሩ ታውቋል።
በስብሰባው ከተሳተፉ የስርዓቱ ወገኖች ከሆኑ ስሞችን ለመጥቀስ ያህል የሳንጃ ወረዳ ኮማንደር እንዳርጋቸው አለሙና ሌሎችን የሚገኙባቸው እንደተሳተፉ ሲገልፅ በዚህ ሁኔታ የሰጉ አንዳአንድ የስርኣቱ ካድሬዎች ደግሞ “በዚህ ስብሰባ ፀረ-መንግስት ተቃውሞ የሚያነሱ ያሉ የአርበኞች ተላላኪዎች ሰርጎ ስለ ገቡ ነው” ሲሉ እንደተሰሙና በዛን ቀን ደግሞ በመቐለ ከተማ የኢህአዴግ ጉባኤ እየተካሄደ እንደነበር የተገኘው መረጃ ጨምሮ አስታውቋል።

No comments:

Post a Comment