Sunday, September 13, 2015

መኢአድ ለጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቤቱታ አቀረበ


መኢአድ በምዕራብ ሸዋ ናኖ ወረዳ ነዋሪ በነበሩ 87 አባወራዎች ላይ በአካባቢው የመንግስት ባለስልጣናት ተፈፅሟል የተባለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የአቤቱታ ደብዳቤ ፃፈ፡፡ ፓርቲው በደብዳቤው እንደገለፀው፤ በወረዳው ከ87 በላይ ሠላማዊ ሰዎች ያለምክንያት ከታሰሩ በኋላ መኖሪያ ቤታቸው እንዲቃጠል ከመደረጉም በላይ አንድ ግለሰብ ተደብድቦ ሲሆን ድርጊቱን በዋናነት ፈፅመዋል ያላቸውን 3 የመንግስት ባለስልጣናትና አንድ ባለሀብት ስም ጠቅሷል፡፡
ጉዳዩን ገለልተኛ የሆነ ኮሚቴ ተቋቁሞ እንዲያጣራ ወንጀሉን የፈጸሙት ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ ቤት ንብረታቸው ለተቃጠለባቸው ግለሰቦች አስቸኳይ መንግሥታዊ እርዳታ እንዲደረግና መንግስት ለተጎጂዎች ተገቢውን ካሣ እንዲከፍል ፓርቲው ጠይቋል፡፡ በቅርቡ ጉዳዩን በተመለከተ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ሪፖርት ማውጣቱ ይታወሳል፡፡

No comments:

Post a Comment