
የትግራይ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ሃላፊና የክልሉ ዳኞች ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም በሙስና ስለተገመገሙ ከሃላፊነታቸው መውረድ አለባቸው ሲሉ የህወሓት ጉባኤተኞች የወሰኑትን ውሳኔ እስከ አሁን ድረስ እንዳልተተገበረ ተገለፀ።
እንደ ምንጮቻችን መረጃ መሰረት የአባይ ወልዱ ሚስት የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም ላለፉት አመታት የትግራይ ክልል የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆነው በሰሩበት ጊዜ በመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ለውጦች ባለማምጣታቸው የተነሳና ጊዜው ያለፈው አስራር በየጽህፈት ቤቱ በነበረበት መሰረት እንዲቀጥል በማድረጋቸው እንደተነቀፉና ሌሎች በፍትህ ቢሮ በተደረገ ግምገማ በከባድ ሙስና የሀገርና የህዝብ ሃብት በማጠፋፋት ስለተገመገሙ በህወሓት ጉባኤተኞች ከሃላፊነታቸው እንዲወርዱ ወስኖ እያለ ባለሉበት የስልጣን እርከን በመቀጠል ላይ እንዳሉ ታወቀ።
አግባብነት የሌለውን የትግራይ ክልል የአስተዳደር አሰራር የታዘቡት አገር ወዳድ የመንግስት መስሪያ ቤት ሃላፊዎችና ምሁራን ወ/ሮ ትርፉ ቀድሞም የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆኖው የተመደቡበት ምክንያት በአቅም በልጠው ሳይሆን የአባይ ወልዱ ሚስት በመሆናቸው ነው። አሁንም በፈፀሙት ጥፋት ከሃላፊነታቸው ተወግደው ጉዳያቸው በህግ ፊት መጣራት እየተገባው በሃላፊነታቸው መቀጠላቸው የስርአቱን አመጣጥ የሚያመለክት እንደሆነ እየገለፁ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል
እንደ ምንጮቻችን መረጃ መሰረት የአባይ ወልዱ ሚስት የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም ላለፉት አመታት የትግራይ ክልል የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆነው በሰሩበት ጊዜ በመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ለውጦች ባለማምጣታቸው የተነሳና ጊዜው ያለፈው አስራር በየጽህፈት ቤቱ በነበረበት መሰረት እንዲቀጥል በማድረጋቸው እንደተነቀፉና ሌሎች በፍትህ ቢሮ በተደረገ ግምገማ በከባድ ሙስና የሀገርና የህዝብ ሃብት በማጠፋፋት ስለተገመገሙ በህወሓት ጉባኤተኞች ከሃላፊነታቸው እንዲወርዱ ወስኖ እያለ ባለሉበት የስልጣን እርከን በመቀጠል ላይ እንዳሉ ታወቀ።
አግባብነት የሌለውን የትግራይ ክልል የአስተዳደር አሰራር የታዘቡት አገር ወዳድ የመንግስት መስሪያ ቤት ሃላፊዎችና ምሁራን ወ/ሮ ትርፉ ቀድሞም የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆኖው የተመደቡበት ምክንያት በአቅም በልጠው ሳይሆን የአባይ ወልዱ ሚስት በመሆናቸው ነው። አሁንም በፈፀሙት ጥፋት ከሃላፊነታቸው ተወግደው ጉዳያቸው በህግ ፊት መጣራት እየተገባው በሃላፊነታቸው መቀጠላቸው የስርአቱን አመጣጥ የሚያመለክት እንደሆነ እየገለፁ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል
No comments:
Post a Comment