Monday, July 20, 2015

ወያኔ በደጋፊወቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑ ተሰማ!


images
አገዛዙ 11ኛዋ ሰአት ላይ በደጋፊወቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑ ተሰማ!
የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች በደጋፊዎቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑን ከውስጥ አወቅ ምንጮች ያገኘናቸው የግምገማ መርጃወች አመላከቱ።የስር አቱ ደጋፊዎችና ታማኝ የሚባሉ ካድሬወች ያነሱት ነጥብ ሲጨመቅ እንደሚከተለው ቀርቧል።
“በተለይ ለእኛ ስለ ወቅታዊ ሁኔታወች ስውር የሆነብን ምክንያት ምንድን ነው፧ እኛም የፓርቲያችን እና የአገራችን ጉዳይ ያገባናል። እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ዜናወችና መረጃወችስ እንዲደርሱን የሚደረገው ለምንድን ነው። እኛ እዚህ ፊትለፊት ከህዝብ ጋር የምንጋጭ ነን። ይህ ቢታሰብበት ጥሩ ነው። እኛ የኢህዴግ አባላት በዚህ ችግር ምክንያት በህዝቡ ዘንድ የሚሰራጨው እና ህዝቡን የሚያደናብሩ ወሬወች ለይተን ህዝቡን እንዴት እናስረዳ፧ ይህ መልስ የሚሻ አንገብጋቢ የወቅቱ ችግራችን ነው። እባካቹህ ይታሰብበት።”

No comments:

Post a Comment