Wednesday, July 1, 2015

ፖሊስ እነወይንሸት በዋስ እንዳይፈቱ ከለከለ

ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2007 ዓ.ም ልደታ ፍርድ ቤት 11ኛ ችሎት ቀርበው በቂሊንጦ ታስሮ ሚገኘው ማስተዋል ፈቃዱ ባለመቅረቡ የአቃቢ ህግ ይግባኝ ሳይታይ ቀርቶአል፡፡ ወይንሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬ እና ቤተለሄም አካለወርቅ ትናንት በዛቻ እና ማስፈራራት ክስ ቄራ ምድብ ችሎት ቀርበው በዋስ እንዲወጡ ቢታዘዝም ካሳንቺዝ ስድስተኛ ፖሊስ ግን ታሳሪዎቹን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡
ጠዋት በልደታ የይግባኝ ሰሚ ችሎት ነገ እንዲቀርቡ የተቀጠሩት እነወይንሸት ለፍርድ ቤቱ ስለእስራቸው ባስረዱበት ወቅት ዳኛዋ “እኔ ታስራችሁ ቅረቡ ብዬ አላዘዝኩም፡፡ በሌላ ክስ መታሰራችሁን ነው የማውቀው፡፡ በሌላ ክስ ዋስ ከተሰጣችሁ ነገ በራሳችሁ መቅረብ ትችላላችሁ፡፡” በማለት ነበር ያሰናበተቻቸው፡፡
እነወይንሽት መንግስት አይኤስአይኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ሰበብ ከሁለት ወር በላይ በህገወጥ እስር የቆዩ ሲሆን፤ ፍርድ ቤት እንዲለቀቁ ባዘዘባቸው ወቅቶች ሁላ ፖሊስ በህገወጥ መንገድ መልሶ አስሮ እያንገላታቸው ይገኛል!

No comments:

Post a Comment