

የሳሙኤል አወቀ ስርዓተ ቀብር ላይ ደርሰው ወደ ደብረማርቆስ ሲመለሱ የነበሩት ለቀስተኞች ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ወደ ደብረማርቆስ እንዳይመለሱ መታገታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለቀስተኞቹ በመኪና እየተመለሱ በነበረበት ወቅት ከቢቸና ወደ ደብረማርቆስ 80 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኝ የትመን የተባለች ቦታ ላይ ፖሊሶች ያስቆሟቸው ሲሆን ‹‹በዚህ ሰዓት መንቀሳቀስ አትችሉም›› በሚል የሾፌሩን መንጃ ፈቃድ ከቀሙ በኋላ ለሚሊሻ አስረክበዋቸው ሄደዋል፡፡ ለቀስተኞቹ የታገቱበት ቦታ ከመኖሪያ አካባቢ የራቀና ጫካ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ለቀስተኞቹ አሁንም ድረስ በበርካታ የሚሊሻ አባላት ተከበው ይገኛሉ፡፡
No comments:
Post a Comment