Monday, June 22, 2015

ዛሬ ቤተ እስራኤላዊያን ሰላማዊ ስልፍ በቴል አቪብ ያደርጋሉ

ዛሬ ቤተ እስራኤላዊያን ሰላማዊ ስልፍ  በቴል አቪብ ያደርጋሉ
ምክንያቱም ባለፍው ቤተ እስራኤላዊ በፖሊስ ተመቶ ነበር ፖሊሱ እስር ቤት መግባት አለበት ብለው ሲጠይቁ የተሰጠው መልስ መጀመሪያ የተማታው ቤተ እስራኤላዊ ነው ፖሊሱ አይድለም የሚል ነበር
ይህን ያስቆጣቸው ቤተ እስራኤላዊያን ዝም ብለው አልተመለከቱም በዛሬው እለት በአደባባይ ይወጣሉ 
አንድ ፍክራ አላቸው ይህም
አንድ ሰው ለሁሉም ነው
ሁሉም ለአንድ ሰው ነው የሚል ነው
የእኛን አንድ ሰው ነካችሁ ማለት ሁላችን ነካችሁ ነው የሚል ነው
በእውነት ሲታይ እንደዚህ አይነት አንድነት ታይቶ አይታወቅም አንድ ሰው ስለተነካ ሁሉም ለእኔ ብለው የሚወስዱት አንድነት
ፖሊሱ ፍርድ ቤት አይቀርብም እንደተባለ የእስራኤል መንግስት የቤተ እስራኤላዊያንን አንድ ነገር አላቸው
ኑ በንግግር እንፍታው እንደራደር ሰላማዊ ስልፍ አትውጡ
ከቤተ እስራኤላዊያን ለእስራኤል መንግስት የተሰጠው መልስ
የሸቀጥ ዕቃ ነው ለድርድር የሚቀርብ የእኛ ወገን የሸቀጥ ዕቃ አይድለም ምንም ንግግር አያስፈልግም የሚል ነው ፖሊስ በተጠንቀቅ ይገኛል
የዛሬውን ሰላማዊ ስልፍ ልዩ የሚያደርገው
የሀይማኖት አባቶች አንድነት ፈጥርው መገኝታቸው
የእስራኤል ጋዜጠኞች ወደ ቤተ እስራኤላዊያን መሆናቸው ብዙ ነጮች አብርው መሳተፋቸው ነው
ቤተ እስራኤላዊያን በእስራኤል ብዙ የተባሉት 190,000 ቢሆኑ ነው በጣም የሚያስደንቀው ግን አንድነት መፍጠራቸውና እስራኤልን የመሰለች ከባድ ሀገር ማስጨነቃቸው ነው
ከእነሱ ብዙ መማር ይቻላል
ይመቻችሁ ብያለሁ ጌቱ

No comments:

Post a Comment