
ለወጣቶቹ መሰደድ ደግሞ ብዙ ምክንያቶች ይነሳሉ አልጄዚራ በድረ-ገጹ ባወጣው ፅሁፍ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ በማለፍ ለኢትዮጵያውያኑ መሰደድ በዋነኛነት የሚነሱ ምክንያቶችን ዘርዝሯል
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት በኢኮኖሚ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሀገሮች መካከልም ስሟ የሚጠራ ቢሆንም ዜጎቿ ግን መሰደድን አላቆሙም በዚህም ምክንያት አብዛኛዎቹ በሚመርጡት ህገወጥ ስደት ብዙዎች እየሞቱ ይገኛሉ
በከተሞች አካባቢ አጥጋቢ የስራ እድል አለመኖሩ, በአብዛኛው የሚሰሩ ስራዎች የዜጎችን ህይወት ወደ ተሻለ ደረጃ ማሸጋገር የሚችል አለመሆኑ, በየጊዜው የኑሮ ውድነት እየጨመረ መምጣቱ እና ሌሎች ብዙ ምክንያቶች ይነሳሉ
አልጄዚራ ባወጣው ፅሁፍ ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ በፖለቲካ ሁኔታ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥራቸው አነስተኛ የሚባል አይደለም ለዚህም እንደማጣቀሻ ጥሩ የስራ እድል የሚያገኙ ዜጎች ከመንግስት የፖለቲካ ሁኔታ ጋር ቅርበት ያላቸው መሆናቸው ይነገራል
ሁላችንም እንደምናውዘቀው በዜጎች ላይ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ በግልፅ የሚታይ እውነታ ነው ነገር ግን ለሚደርሰው ጥፋት በዋነኛነት ተጠያቂ ሊሆን የሚችለውን አካል ለእያንዳንዳችን ግንዛቤ እንተወውና በሁላችንም ዘንድ ምን መፍትሄ ማምጣት ይቻላል?
ሁላችንም እንደምናውዘቀው በዜጎች ላይ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ በግልፅ የሚታይ እውነታ ነው ነገር ግን ለሚደርሰው ጥፋት በዋነኛነት ተጠያቂ ሊሆን የሚችለውን አካል ለእያንዳንዳችን ግንዛቤ እንተወውና በሁላችንም ዘንድ ምን መፍትሄ ማምጣት ይቻላል?
ማን ምን ቢያደርግ ይሻላል ትላላችሁ? በኩራት ታሪክ እየጠቀስን ብቻ የሀገርን ገፅታ መለወጥ እንችላለን?
የኛ ሀገራዊነት ስሜት ስፖርታዊና ስፖርታዊ ባልሆኑ ውድድሮች ላይ ብቻ የሚንፀባረቅ አይመስላችሁም?
የእናንተ ሀሳብ ምንድነው?
No comments:
Post a Comment