Tuesday, April 21, 2015

ሰበር ዜና ህዝብ በወያኔ ላይ በአዲስ አበባ ተቃውሞውን እያሰማ ነው

ሰበር ዜና
አሁን የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ከተማ ውስጥ ማን እንደበተነው ያልታወቀ ነገ የስራ ማቆም አድማ እና ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ወረቀት ተበትኗል! በየታክሲውና ከተማ ውስጥም መነጋገሪያ እንደሆነ ታውቋል።
ፖሊስ ሰልፈኛው ወደ ሜክሲኮ እንዳይሄድ ለማገት ቢጥርም ህዝቡ ግን አንቆምም ብሎዋል
ሰልፉ አዲስ አበባን ሲዞር ሊውል ነው!
አሁን ሰልፈኛው ወደ ከቄራ ወደ ሜክሲኮ እየዞረ ነው!
ፖሊስ ምንም ማድረግ ስላልቻለ ሰልፉ በሞተር እየተመራ ነው፡፡ በርካቶች በስሜት፣ በቁጭት እየተቀላቀሉት ነው፡፡ መፈክሮች፣ ለቅሶ፣ መዝሙር፣ ጩኸት እየተሰማ ነው!
አሁንም በርካታ እናቶች፣ ወጣቶችና ሌሎችም እያለቀሱ ሰልፉን እየተቀላቀሉ ነው! የሰልፈኛው ቁጥር እየተበራከተ ነው፡፡ ኢህአዴግ ከፍተኛ ተቃውሞ እየገጠመው ነው! የኢህአዴግ ናቸው የተባሉ ነገሮች ሁሉ እየተቀዳደዱ ነው!
መንግስት የሌለው ኢትዮጵያ ብቻ ነው
አዲስ አበባ ህዝቡ ያለአንዳች ቀስቃሽ ለሰማዕታቱ ሀዘኑን ለመንግስት ቸልተኝነት ተቃውሞውን እየገለፀ ነው።
በጉልህ ተፅፈው ከሚታዩት መፈክሮች ውስጥ ”ሉዓላዊነት ማለት የትም ቦታ ያሉትን ዜጎቻችንን መብት ማስከበር ነው”11173407_959193090780198_3490740387873963160_n 11150143_678342725645299_5875406239496253050_n 1908198_824771097630671_3394828389672125741_n 11173407_959193090780198_3490740387873963160_n

No comments:

Post a Comment