በጎጃም ሸበል በረንታ ወረዳ ባመጹ አርሶ አደሮችና በመንግስት ሃይሎች መሃል ዛሬ ጠንከር ያለ ግጭት መቀስቀሱ ተሰማ። ከወራት በፊት መሳሪያቸውን ይዘው ወደ ጫካ የሸፈቱትን አርሶ አደሮች ለማጥቃት ሲንቀሳቀስ የነበረው የመንግስት ሃይል ዛሬ በአንሻቢና ቀበሌ አድፍጦ በመጠበቅ በአርሶ አደሮቹ ላይ ተኩስ በመክፈቱ ግጭቱ ሊቀሰቀስ መቻሉ ታውቋል። በእስከአሁን የሸበል በረንታ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ አባትይሁን አስረስ መገደላቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ሁለት ፖሊሶችም ክፉኛ መቁሰላቸው ታውቋል። ከአርሶ አደሮቹ አስናቀ የምወደውና ለጊዜው ስማቸው ያልተገለጹ አርሶ አደር በግጭቱ መገደላቸው ተገልጿል።ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የተኩስ ልውውጡ ቀጥሏል። በተመሳሳይ በጎንደር ጭልጋ ሳምንታት ያስቆጠረው አለመረጋጋት በአርሶ አደሮች አመጽ ተባብሷል። የመንግስት ሃይሎች ከሸፈቱ አደሮች ጋር በጭልጋ ግጭት ውስጥ መሆናቸው ታውቋል። በአከባቢው ትምህር ቤቶች እንደዘጉም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ሁኔታውን በመከታተል ተጨማሪ መረጃዎችን እናቀርባለን።
Monday, November 23, 2015
በጎጃም ሸበል በረንታ ወረዳ ባመጹ አርሶ አደሮችና በመንግስት ሃይሎች መሃል ዛሬ ጠንከር ያለ ግጭት መቀስቀሱ ተሰማ።
በጎጃም ሸበል በረንታ ወረዳ ባመጹ አርሶ አደሮችና በመንግስት ሃይሎች መሃል ዛሬ ጠንከር ያለ ግጭት መቀስቀሱ ተሰማ። ከወራት በፊት መሳሪያቸውን ይዘው ወደ ጫካ የሸፈቱትን አርሶ አደሮች ለማጥቃት ሲንቀሳቀስ የነበረው የመንግስት ሃይል ዛሬ በአንሻቢና ቀበሌ አድፍጦ በመጠበቅ በአርሶ አደሮቹ ላይ ተኩስ በመክፈቱ ግጭቱ ሊቀሰቀስ መቻሉ ታውቋል። በእስከአሁን የሸበል በረንታ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ አባትይሁን አስረስ መገደላቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ሁለት ፖሊሶችም ክፉኛ መቁሰላቸው ታውቋል። ከአርሶ አደሮቹ አስናቀ የምወደውና ለጊዜው ስማቸው ያልተገለጹ አርሶ አደር በግጭቱ መገደላቸው ተገልጿል።ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የተኩስ ልውውጡ ቀጥሏል። በተመሳሳይ በጎንደር ጭልጋ ሳምንታት ያስቆጠረው አለመረጋጋት በአርሶ አደሮች አመጽ ተባብሷል። የመንግስት ሃይሎች ከሸፈቱ አደሮች ጋር በጭልጋ ግጭት ውስጥ መሆናቸው ታውቋል። በአከባቢው ትምህር ቤቶች እንደዘጉም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ሁኔታውን በመከታተል ተጨማሪ መረጃዎችን እናቀርባለን።
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment