በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተግባራዊ እንዳይሆን የተቃውሞ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ከነበሩ የኦሮሚያ ተወላጅ ተማሪዎች መካከል የፊዴራል ፖሊስ ሰራዊት አባላት ወደ ዪኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ በመግባት ሶስት ተማሪዎችን መግደላቸውንና ብዙዎችን ማቁሰላቸው እየተሰማ ነው ።
በኢትዮጵያ የተከሰተዉ ድርቅ በአስከፊ ሁኔታ እየተባባሰ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን መግለጫን ዋቢ በማድረግ ዓለም አቀፉ የዜና አውታር ቢቢሲ ‹‹ በጣም አስደንጋጭና አስፈሪው የኢትዮጵያ ድርቅ ›› በማለት ዘግቧል። እንደዘገባዉም ከሆነ በአሁን ሰዓት 15 ሚልዮን ኢትዮጵያዊን ለከፍተኛ የርሃብ አደጋ ተጋለጠዉ የገኛሉ። የርሃብ አደጋዉ የተከሰተባቸዉ ቦታዎችም በየቀኑ ሁለት ህፃናት ህወታቸዉ እንደሚቀጠፍ መረጃዉ ያመለክታል። በአንፃሩ የመንግስት የዉጪ ጉዳይ ሚስጥር የሆኑት ዶክተር ቴውድሮስ አድሃኖም በሃገራቺን የተራቡት ሰዎች ቁጥር 8 ሚሊዮን ብቻ መሆኑን ይህም ጉዳይ የማይደንቅና አሳሳቢ እንዳልሆነ በትላንተናዉ ለት በአሜሪካ ድምጽ ራድዮ ባደረጉት ቃለ መጠየቅ ተናግረዋል።
በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ቢቢሲ ስለ 15 ሚሊየን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ስለሚፈልጉ ዜጎች መዘገቡን ተከትሎ መንግስታችን የቢቢሲ ዘገባን በመቃወም ለኢንግሊዝ መንግስት የቅሬታ ደብዳቤ ማስገባቱ ተሰምቷል። ይሁንና የዝናብ እጥረት እነደሚኖር፣ ድርቅ እንደሚሆን፣ ሰፊ ረሀብ እንደሚኖር ባለፉት 6 ወራት የተባባሩት መንግስታትን ጨምሮ በማስጠንቀቂያ መልክ በተለያዩ አለምአቀፍ ድርጅቶች ሲነገር ቆይቶአል፡፡ ገበሬውም ተፈጥሮ በለገሰቺዉ ልማድ በመታገዝ ችግሩ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ተናግሯል፡፡ መንግስት የዚህን ችግር አሳሳቢነት ከግምት ዉስጥ በመክተት ወደመፍትሄ ከመንደርደር ይልቅ ለከሰረዉ ፖለቲካዉ ማጣፈጫ ነበር ያደረገዉ፡፡ እንደማሳያነት ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጊዜዉ ስለድርቁ እንዲህ ማለታችዉ ይታወሳል : ድርቅ ብርቅ አደለም አውስትራሊያና ካሊፎርንያረም ደርቀዋል አክለዉም ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ቺላለች የማንንም እርዳታ አያሻንም በማለት ከተራበዉ ኢትዮጵያዊ ጭንቀት ይልቅ የመንግስትን የምግብ ፖሊሲ ማሞካሸትን መርጠዉ ወርደዋል፡፡ ሌላው አቶ ሬድዋን ሁሴን አፋር አካባቢ ከብቶች ያለቁት እረኞቹ ወደ ውሀ ስላልወሰዱዋቸው ነው በማለት ችግሩን ለማዳፈን ብሎም የችግሩን መንስኤ ነብስ በማያዉቁ እረኞች ላይ ደፍድፈዉታል፡፡
ታድያ እዉነት እና ንጋት እንዲሉ ይሄዉ ችግር ተስፋፍቶ አሁን ካለበት አስከፊ ሁኔታ በመድረስ በአሁን ሰዓት በአማካኝ 13% የሚደርሰዉ ኢትዮጵያዊ የዚህ አስከፊ ችግር ሰለባ ሆኗል፡፡ ይህ አስከፊ ሁኔታ በትጋረጠበት ሰዓት መንግስት ይህንን አሳሳቢና ጊዜ ሊሰጠዉ የማይገባዉን ጉዳይ ወደጎን በመተዉ የብአዴን 35ኛ ዓመትን ለማክበር ከ300 ሚልዩን ብር በላይ በመመደብ ላይ ታች ማለቱ ገዢዉ ፓርቲ ከሀገሩ ሕዝብ ችግር ይልቅ አመታዊ የፖለቲካ ዲስኮ እንድሚያስጨንቀው ተግባራዊ ማሳያዉ ነዉ፡፡ ይህ ጉዳይ የተፈጥሮ ሳይሆን በአንድ ጎሳ የበላይነት የታነፀዉ መንግስት ጊዜውን ተከትሎ ለሚከሰት ድርቅ ተግባራዊ መፍትሄ የሚሆን ፖሊሲ መቀመር በአለመቻል የሚከሰት ችግር ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ጉዳይ ሀይለስላሴንና ደርግን የኮነንባቸውን ነጥቦች በማስታወስ መንግስት ዳንኪራዉን ትቶ ወደ ተፈተረዉ ችግርና አፋጣኝ መፍትሄዎች ልቡን ያዙር! ፖለቲካ አላፊ ነው! ህዝብና ታሪክ ግን ለዘለአለም ይኖራሉ!