Sunday, May 17, 2015

ዓረና መድረክ በመቐለ ማዘጋጃ ቤት ኣዳራሽ የተጠራ የህዝብ ስብሰባ የተሳካና ሁሌ በዓረና-መድረክ ታላቅ ህዝባዊ ድጋፍ ኣንጀታቸው እርር የሚሉ ህወሓቶችም ድንጋጤኣቸው ለከት ኣጥተውለት ያሳበዳቸው መድረክ ሁኖ ኣልፏል

ቅዳሜ 08 / 09 / 2007 ዓ/ም በዓረና መድረክ በመቐለ ማዘጋጃ ቤት ኣዳራሽ የተጠራ የህዝብ ስብሰባ የተሳካና ሁሌ በዓረና-መድረክ ታላቅ ህዝባዊ ድጋፍ ኣንጀታቸው እርር የሚሉ ህወሓቶችም ድንጋጤኣቸው ለከት ኣጥተውለት ያሳበዳቸው መድረክ ሁኖ ኣልፏል።
ስብሰባው የተከፈተው በትጥቅ ትግሉ የተሰዉ ሰማእታትና በሊብያ በኣያኤስ ኣያኤስ የታረዱ ወገኖቻችን የኣንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ነበር።
በስብሰባው የዓረና-መድረክ ኣማራጭ ሃሳቦች፣ የገዢው ፓርቲ ድክመቶች፣ ዓረና-መድረክ ያሉት ምርጥምርጥ የመፍተሄ ሃሳቦች ቀርበዋል። ህወሓትም ካድሬዎችዋን ልካ ከፍተኛ ተሳትፎ ኣድርጋለች።
ከህዝብ ከቀረቡ ሃሳቦች ህወሓት የምትባል የድሮ ድርጅት ኣሁን እንደሞተች፣ እንደጠፋች፣ ኣሁን ያለችው ህወሓት ከድሮዋ ህወሓት በፍፁም የማይገናኙና የኣሁንዋ በድሮዋ ህወሓት ስም ለመነገድ እየሞከረች ያለችው ፎርጅድ (ቓንጫ መርዓት፣ ኣሻንጉሊት) እንደሆነች ታላላቅና ወጣት ተሳታፊዎች ድምዳሜ የደረሱበት ሁኔታ በግልፅ ቋንቋ ገልፀዋል።
ህወሓት ስብሰባው እንዳይ ሳካ መጀመርያ ከሰዓት ሰልፍ እንደሚያደርጉ በመኪና የቀሰቀሱ ቢሆኑም ህዝቡ ለዓረና-መድረክ ቅስቀሳ ያሳየው ታላቅ ድጋፍ በመደንገጣቸው ከምሽቱ 2 ስዓት ጀምረው ቤት ለቤት እየዞሩ ሰለማዊ ሰልፉና ስብሰባው ለጥዋት እንደተቀየረና ማንኛውም ኑዋሪ የግድ መገኝት እንዳለበት ኣዘው ነበር።
ይህ ሁሉ ኣድርገው ህዝቡ ወደ ስብሰባው መጣና ኣንጀታቸው ቅጥል፣ እርር ፣ ድብን ኣሉ።
የህወሓት የቀበሌ ካድሬዎችም በኣዳራሹ መግብያ በር ኣጠገብ ሁነው የገባው እየመዘገቡ፣ ፎቶ ግራፍ እያነሱ ዋሉ።
ስብሰበው የዓረና-መድረክ ኣማራጭ ፖሊሲዎች በመገባ ወደ ተሳታፊው እንዲደርሱ ተደርገዋል።
ህወሓቶች ምክሬን ተቀበሉ።።። ህዝቡ በጣም ጠልቷቹሃል። ስለዚህ የህዝብ ድምፅ ለመቀበል ተዘጋጁ፣ መድረክም ለሰራቹት ጥፋት ሁሉ ይቅር ሊላቹና በሚመሰርተው ሃገራዊ እርቅ የሚመሰረት መንግስት ኣካል ያደርጋቹሃል። ይህ ሲባል ከሁሉም ሰለማዊ ተቃዋሚ ድርጅቶች፣ ከትጥቅ ትግል የመረጡ ወገኖች፣ በውስጥና በውጭ ኣገር ከሚኖሩ ኢትዮዽያውያን ምሁራት የተውጣጣና የሽግግር መንግስት ኣካል ት ሆናላቹ።
ኣለበለዝያ እንደለመድነው ኮሮጆ ዘርፈን በስልጣን እንቆያለን የሚል ቅዠት ካላቹ ግን ለናንተም ጥሩ ኣይደለም፣ ለሃገሪቷም ኣይጠቅምም።
የትግራይ ህዝብ ግን ምርጫው በግልፅ ቋንቋ ዓረና-መድረክ እንደሆነ እየተናገረ ነው።
ነፃነታችን በእጃችን ነው..!
IT IS SO...!

No comments:

Post a Comment