ታዛቢዎችና ተቃዋሚ ፓርቲ ኣባሎች በማዋከብ ተጀምሮ ያለ ተቀዋሚ ፓርት ታዛቢ ቆጠራ የተጠናቀቀው ምርጫ 2007 ኣምባገነኑ የሕወሓት ስርዓት ያለ ህፍረት ኣይኑን በጨው ኣጥቦ ኣሸነፍኩኝ ለማለት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦር የወያኔ ኣጋር ፓርቲ እስኪመስል ድርስ ሙሉ ድጋፉን ለወያኔ የሰጠው ቦርድ ስለ ምርጫው ዴሞክራሲነት ለማዉራት ሞራሉ እንካ ባይኖሮው ነገር ግን ወያኔ ከዓለም መንግስታት ለየት የሚያደርገው የክህደትና የማጭበርበር ስልቱ ይህንን የሞተ ቦርድም መግለጫዎች ሲያጎርፍ ተመልክተናል፡፡
ወያኔ እንደ ሰለማዊ ትግልን የሚፈራው ነገር እንደሌለ ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚያስገለብጠው ኮሮጆ እና የሚያዋክባቸው ተቆዋሚ ፓርቲዎችን በማየት የሚገለፅ ሲሆን ኣሁንም ግን ወያኔ ሃገሪትዋ በማጭበርበር ዳግም ለመግዛት ኣቅዶዋል፡፡
በሰለማዊና ነፃ ምርጫ ተወዳድሮ ኣሸንፎ የማያዉቀው ኮሮጆ ገልባጩ ወያኔ ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ወደ ጦርነት ለማስገባት እየጣረ ይገኛል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን ኣንድነታችን በማጠናከር ወያኔን ለመገልበጥ መዘጋጀት ኣለብን፡፡
ሁሌም ቢሆን ወያኔ ኮሮጆ በማስገልበጥና እና ወላጆቻችን እዚች ንብ ላይ ምልክት ኣድርጉ እየተባለ እየተዋከበ ብግድ ምልክት ቢያደርግም እኛ ተቀዋሚ ፓርቲዎች በተለይ ሰማያዊ እና መድርክ በቅርቡ ዉህደት ፈጥራችሁ ህዝባችሁን እንድታስደስቱትና በምርጫ 2012 ዓ/ም ለመወዳደር እንድትዘጋጁ እያልኩኝ በወያኔ ድራማዊ የምርጫ ሂደት ፍፁም ፀረ ዴሞክራሲ በሆነ ምርጫ ተስፋ መቁረጥ እንደሌለባችሁ ኣሳስባለሁኝ፡፡
በእርግጥ የወያኔ መንግስት የተንኮልና የማጭበርበር እንጂ በህዝብ ተቀባይነት የሌለው በምርጫ ሁሌም እየተሸነፈ በጠመንጃ እና በምርጫ ቦርድ ትብብር ስልጣኑን የሚደላድል ወያኔ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያወግዘው ይገባል፡፡
ወያኔ የበረሓ ባሕሪዉን ያልለቀቀው ገና 25 ዓመት ኣዲስ ኣበባን ከትሞ የዘመናዊነት ኣስተሳሰብ ያልተላበስ ሁሌመ በጫካ ሕግጋትን እቺ ሃገር ለማተራመስ እንዳቀደ ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ዘላለሙ እንደዋሸ ለሞኖር የሚያደርገው ጉዞ የሚያከትምበት ዘመን ሩቅ እንደማይሆን መገመቱ ኣያስቸግርም ኣሉ የተባሉት ተቀዋሚፓርቲዎች ልዩነታቸው ኣጥብበው ፀረ-ወያኔ ከተሰለፉ ፡፡
ኑና ሁላችንም ፀረ-ወያኔ እንሰለፍ፡፡
No comments:
Post a Comment