Monday, September 5, 2016

የትግራይ ክልል መንግስት የአማራ ህዝብ የዘር ማፅዳት ፈፅሞብኛል የሚል ይፋዊ መግለጫ አወጣ።


በአማራ ክልል የሚገኙ ሁሉም የትግራይ ተወላጆችንም የተከፈለው ሁሉ ተከፍሎ ከአማራ ክልል እንዲወጡ ለማድረግ እየተሰራው ነው እንደ መግለጫው።
በትግራይ ክልል መንግስ የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮሚቴ በሰሞኑ በአማራ ክልል በተነሳው እና በርካታ (ከ200 በላይ ሰዎችን ህይወት ለጠፈበት) በባህር ዳርም ይሁን በጎንደርግጭት የትግራይ ተወላጆች ዘራቸው እንዲጠፋ በዘር ተለይተው ጥቃት ደርሶባቸዋል ነው ያለው በትግራይ online በተደረገው ምስልና ፅሁፍ መግለጫ።
ይሁና ሁላችንም እንደምናውቀው በጎንደርም ይሁን በባህርዳር እንዲሁም በመተማ ትግሬ በመሆናቸው ሳይሆን በስርዓቱ ተጠግተው መዥገር የሆኑ በዝባዥ የብአዴንም ይሁን የትግራይ አባላት ላይ ህዝቡ ድንገይ በመወርወር ስሜቱን ገልጿል። በርካታ ህይወትም ተቀጥፏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የአማራ ክልል መንግስት ባለፈው እስካሁን በትግሬነት ብቻ ያነጣጠረ የዘር ማፅዳት(Ethnic cleanising) ቀርቶ ድብደባ እንኳን እንዳልተፈፀመባቸው የጎንደሩን ማስረጃ ማቅረቡ ይታወሳል።
እኔ በግሌ ይህ የትግራይ መንግስት አስፀያፊና የውንብድና መግለጫ ግን ከእንግዲህ የአማራን ህዝብም ለራሲ ህልውና እንዲቆም ማስጠንቀቂያ ደወል ይመስለኛል።
2.4 ሚሊዮን አማራ እንኳን ከምድረ ገፅ ሲጠፋ የወቀስን ህወሃትን እንጀ የትግራይን ህዝብ አልነበረም።ከእንግዲህ ግን እኛም ማምረር ሳይኖርብን አይቀርም።

No comments:

Post a Comment