Friday, September 16, 2016

ወያኔ መንግስት በኮንሶ በሚኖሩ አማራ ህዝብ ላይ ጥቃት እየፈፀመ ነው


*ከ60 ዓመታት በላይ በኮንሶ የኖሩ፣ ቋንቋቸው ኮንሶ የሆኑ ከ200 በላይ የአማራ ብሔር ተወላጆች ማሳቸው በእሳት ነዶ፣ ቤታቸው ተቃጥሎ ተፈናቅለዋል። በ4 አይሱዙ ጭነት መኪና ሼሌ ላይ የተበተኑት አማሮችን ኮንሶዎች ምግብ እና መጠለያ እየሰጡ ረድተዋቸዋል።
የኮንሶን የአስተዳደር ጥያቄን ወደ ብሔር ግጭት ለመውሰድ በገዢው ስርዓት ህወሓት_ደኢህዴን የተፈጸመ ሴራ እንደሆነ ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የአማራ ብሔር ተወላጆች ዛሬ አርባምንጭ እንደገቡ ታውቋል። ከሰሞኑ ከ50 በላይ ሰዎች በኮንሶ መገደላቸው ይታወቃል።
በሱማሌና በጋንቤላ ክልልም እንዲሁ አማራ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በመደረግ ላይ ነው ማምሻውን ደሞ በአርባ ምንጭ ከተማ የአፄ ቴውድሮስን ፎቶ የለጠፉ የባጃጅ ሹፌሮች በመደብደብ ላይ ናቸው ወያነ ሆን ብሎ የአማራውን መደራጀትና ትግል ለማዳከም ሲል ከተለያዩ ክልል ተወላጆች ጋር አማራውን የሚያነካክስ ተግባር በመፈፀምና በማስፈፀም ላይ ነው። የአማራ ህዝብ ሆይ ባለህበት ተደራጅ ተራዳዳ አለዛ የወያነ ትግሬ አንተን ከማጥፋት ወደኋላ አይልም።

No comments:

Post a Comment