በደቡብ ጎንደር ዞን፣ በደራ ወረዳ – በአርብ ገባያ በአርብ ገበያ በመከላከያና በአርሶ አደሮች መካከል የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ ነው፡፡የግጭቱ ምክንያት ትላንት ምሽት ከእስቴ ወረዳ የተጫነ 90 ኩንታል ጤፍ ጭኖ የመጣ መኪና አርብ ገበያ ሲደርስ በህዝብ እንዲቆም ከተደረገ በኋላዳ መጣበት እንዲመለስ መደረጉ ነው፡፡
ህዝቡ ከእንግዲህ ወዲያ ጤፍም ሆነ ሌላ ማናቸውም እህል ከአካባቢያችን ወደ ሌላ ስፍራ አይንቀሳቀስም በሚል ተቃውመው መኪናውን ማስቆማቸውን ያይን ምስክሮች የገለጡ ሲሆን ከጥቂት ሰዓታት እገታ በኋላ ወደ መጣበት እስቴ ወረዳ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት ዛሬ ረፋዱ ላይ በአርሶ አደረ እና መከላከያ አባላት መካከል የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ ከስፍራው የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአምባ ጊዮርጊስ በተደረገው ግጭት 18 የመከላከያ አባላትና በአርሶ አደሮች ደግሞ 30 ያህሉ መገደላቸውን ተከትሎ በዛሬው ለት የአጋዜ ታጣቂዎች በከተማው ወጣቶች ላይ መጠነ ሰፊና ዘግናኝ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ከእርምጃው የተረፉ በርካታ የከተማው ወጣቶች ጫካ መመሸጋቸውም ታውቋል፡፡
ህዝቡ ከእንግዲህ ወዲያ ጤፍም ሆነ ሌላ ማናቸውም እህል ከአካባቢያችን ወደ ሌላ ስፍራ አይንቀሳቀስም በሚል ተቃውመው መኪናውን ማስቆማቸውን ያይን ምስክሮች የገለጡ ሲሆን ከጥቂት ሰዓታት እገታ በኋላ ወደ መጣበት እስቴ ወረዳ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት ዛሬ ረፋዱ ላይ በአርሶ አደረ እና መከላከያ አባላት መካከል የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ እንደሚገኝ ከስፍራው የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአምባ ጊዮርጊስ በተደረገው ግጭት 18 የመከላከያ አባላትና በአርሶ አደሮች ደግሞ 30 ያህሉ መገደላቸውን ተከትሎ በዛሬው ለት የአጋዜ ታጣቂዎች በከተማው ወጣቶች ላይ መጠነ ሰፊና ዘግናኝ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ከእርምጃው የተረፉ በርካታ የከተማው ወጣቶች ጫካ መመሸጋቸውም ታውቋል፡፡

No comments:
Post a Comment