Wednesday, June 29, 2016

በኢትዮ ኤርትራ ድንበር ላይ ዛሬ ማለዳ ላይ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች በመታየት ላይ ናቸው ተባለ


ከባድ መሳሪያ የተያዩ ወታደራዊ ሎጀስቲክንና የዓየር መቃወሚያዎችን ጨምሮ ለጊዜው ምንነታቸው በግልፅ ሊለዩና ሊታወቁ ያልቻሉ ቁሶችን የጫነ ኮምቮይ ከመሀል አገር ተነስቶ ወደ ፆረና እያመራ ነው። ዳግም ግጭት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት ያደረባቸው በሁለቱ ሀገራት ድንበር አቅራቢያ በሚገኙ ከተሞች የሚኖሩ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው በመሄድ ላይ መሆናቸውን መረጃውን ካከባቢው ያደረሱን ያይን እማኞች በመናገር ላይ ይገኛሉ ። የብዙሀኑን ፖለቲከኞችና ወታደራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች ትናንሽ ትንኮሳዎችና ግጭቶች ወደ ለየለት ጦርነትና እልቂት መሸጋገራቸው አይቀርም የሚለውን ግምትና ጥርጣሬ ትክክለኛነት በሚያረጋግጥ መልኩ በሁለቱ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል ለህዝባቸው ይፋዊና ግልፅ ባልሆነ መልኩ በከፍተኛ ወታደራዊ ሚስጥርነት ተይዞ በመከናወን ላይ የሚገኘው የጦርነት ዝግጁነት የሚፈለገውን የማጥቃትና የመከላከል አቅሙ ተገንብቶ እስኪጠናቀቅ ድረስም ሁለቱም መንግስታት ዝምታን መርጠዋል ። ይህን ተከትሎ በዚህ ውጥረትና አለመረጋጋት በሰፈነበት የድንበር አዋሳኝ ክልሎች እና ቀበሌዎች ከጠላት ወገን ሊደርስ የሚችለውን ወረራና የማጥቃት እርምጃ ለመከላከልና ሲመችም ድንገተኛ አደጋዎችን ለመጣል ሲባል በአካባቢው የሚደረገው ያልተለመደ እንቅስቃሴና ወታደራዊ ሰፈራ ያሳሰባቸው ሰላማዊ ዜጎችም ለሀጥያን የመጣ ለፃድቃን ይተርፋል በማለት የመኖሪያ ስፍራቸው ባጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ጦርነት አውድማ ከመቀየሩ በፊት ከብቶቻቸውንና ንብረቶቻቸውን በመያዝ ወደ አጎራባች ቀበሌዎች በገፍ በመሰደድ ላይ ይገኛሉ። በተያያዘ መረጃ የኢህአዴግ መንግስት በስሩ በሚገኙ ሚዲያዎቹ በኩል በተደጋጋሚ ይፋ እንደሚያደርገው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አርበኞች ግንቦት ሰባት እያገኘ የመጣው ህዝባዊ ድጋፍና የተደራጀ ጦር በይፋ ያሳስበኛል ለማራምደው ስርዓትም የሽብርና የስጋት ምንጭ ሆነዋል በማለት መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ነው

Friday, June 24, 2016

በደቡብ ጎንደር ሊቦ ዓውራጃ አቶ አረጋ የተባለ የከምከም ወረዳ ነዋሪ፥ 6 የወያኔ አፋኝ ቡድኖችን ረሽኖ ስናይፐር ጠመንጃ ማርኮ ወደ ጫካ መሰወሩ ተሰማ፥


ጎንደር በሕዝቡና በወያኔ ሕወሓት አገዛዝ መሃከል ያለው ውጥረት በእየአቅጣጫው እየጨመረ ነው፥ በስርዓቱ አገልጋዮች ላይ የሚወሰደው ቆራጥ እርምጃም ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጠናክሮ ቀጥሏል፥
ጀግናው የጎንደር ሕዝብ የወያኔን ሰቆቃ የምንሸከምበት ትካሻ የለንም በማለት፥ የሚሰነዘርበትን የኃይል ጥቃት በነፍጥ በመመከት ፍትህን በእጁ ማስከበሩን ተያይዞታል።
በሊቦ አውራጃ የከምከም ወረዳ ነዋሪ በሆነው አቶ አረጋ የተባለ ታጣቂ በወያኔ ዓፋኝ ጓዶች ላይ የተወሰደው ቆራጥ እርምጃና የጀግንነት ተጋድሎ የገዥዎች በደልና ግፍ የወለደው በመላው ኢትዮጵያ የሚብላላው የለውጥ ጥንስስ፥
በመሃል ጎንደር ታጣቂ አምሳሉ ተሾመ ሊያፍኑት በመጡ 6 የወያኔ ወታደሮች ላይ እርምጃ ወስዶ ራሱን በመሰዋት የጀመረው፣ በዳባትና በበየዳ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ በላይ አርማጭሆ ፈረስ_መግሪያ ቀበሌ ላይ የወያኔን አፋኝ ኮማንደር ረሽኖ 40 ጎራሽ መትረየስ ማርኮ የነጻነት ታጋይ አርበኞችን የተቀላቀለው ወጣት አልብሰው ወልደዝጊ ከሰራው ጀብዱ የቀጠለ፥ የእምቢ አሻፈረኝ የነጻነት ተጋድሎ ዛሬም ስድስት ፖሊሶችን ገድሎ 1 ስናይፐር ጠመንጃ ማርኮ ከአካባቢው ተሰውሯል የሚለውን ዜና ከደቡብ ጎንደር ከአዲስ ዘመን ዓካባቢ አሰምቶናል።
ሞት ለወያኔ ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች ታግተው ለዘረኛውና አፋኙ የወያኔ ቡድን ተላልፈው የተሰጡበትን ሁለተኛ ዓመት


የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች ታግተው ለዘረኛውና አፋኙ የወያኔ ቡድን ተላልፈው የተሰጡበትን ሁለተኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በሲዊዲን እስቶክሆልም እንዲህ ታስቦ ውሏል!!!
የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ይዞለት የተነሳውን አላማ ከግብ ላማድረስ በቆራጥነት አበክራን መስራት እንዳለብን እና ለተቀጣጠለው ለጻነት አና ዲሞክራሲ እንዲሁም ሰባዊ መብት ለማስመለ ለሚደረገው ትግል ለአንድ ጌዚ እና ለመጨረሻ ወያኔን በማስወገድ ለመላ የአራችን ህዝቦች በእኩልነት ላይ የተመስረተች ሀገር ለመፍጠር አንዳርጋቸው የጀመረውን የቆመለትን አላማ ከዳር ለማድረስ በምንችለው እራሳችንን የትግሉ አካል በማደረግ የዚግነት ግዴታችን መወጣት እንዳለብን ሁላችንም አንዳርጋቸው ፅጌ ነን !!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Wednesday, June 22, 2016

የመብት ጥሰት ደርሶብኛል ብለው ወደ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደጃፍ ከደረሱ ከ1 ሺህ 419 አቤቱታዎች 999 ያህሉ ተቀባይነት እንዳላገኙ ተሰማ


ባለፉት 11 ወራት ከዜጐች ለኮሚሽኑ የቀረቡ አቤቱታዎች በቁጥርም በዓይነትም ካለፉት ጊዜያት ጋር ሲነፃፀሩ መብዛታቸውን ሰምተናል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር እንዳሉት ከቀረቡት 1 ሺህ 419 አቤቱታዎች መካከል 999 ያህሉ ተቀባይነት ያላገኙባቸው ምክንያቶች መካከል፣ አቤቱታዎቹ ከወንጀል ወይም ከሙስና ጋር የተገናኙ መሆናቸው አንዱ ምክንያት ነው፡፡
በተጨማሪም ከመልካም አስተዳደር ጋር በተገናኘ የደረሱ ተደራራቢ በደሎች ሆነው ከዚህ ቀደም ለእንባ ጠባቂ የቀረቡ ሆነው ስለተገኙ አቤቱታዎቹ በኮሚሽኑ ተቀባይነት አላገኙም ብለዋል፡፡
አንዳንዶቹ አቤቱታዎች ደግሞ የቀረቡት ከአዕምሮ መታወክ እና ከስነ-ልቦና ችግር የመነጩ ሆነው አግኝተናቸዋል፡፡ በመሆኑም 999ኙ አቤቱታ አቅራቢዎች የተሸኙት የምክር አገልግሎት ብቻ ተሰጥቷቸው እንደሆነ ከኮሚሽነሩ ሰምተናል፡፡
ወሬውን የሰማነው ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሚሽኑን የ11 ወር እቅድ አፈፃፀም ሲመረምር ነው፡፡
የመብት ጥሰት ደርሶብኛል ብለው በግልና በቡድን ለኮሚሽኑ አቤት ካሉት 1 ሺህ 419 አቤቱታ አቅራቢዎች መካከል ተቀባይነት ያገኙት 330 ብቻ መሆናቸውን ሰምተናል፡፡
የቀረቡትን ቅሬታዎች በመመርመርና በማስማማት መፍትሄ የተሰጣቸው ለ264 አቤቱታዎች ነው፡፡
ሌሎች 47 አቤቱታዎች በመረጃ እጦትና በተለያየ ምክንያት እንዲዘጉ ተደርጓል፡፡
ቀሪዎቹ 78 አቤቱታዎች ደግሞ ጉዳዩ ያገባቸዋል ወደተባሉ መሥሪያ ቤቶች በደብዳቤ መሸኘታቸውን ኮሚሽነሩ ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ተናግረዋል፡፡
አሁንም በምርመራ ላይ ያሉ 19 አቤቱታዎች መኖራቸውን የተናገሩት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ባለፉት 11 ወራት ከዜጐች የሚቀርቡ አቤቱታዎች በቁጥርም ሆነ በዓይነትም ጨምረዋል፡፡ አብዛኞቹም የመልካም አስተዳደር እጦት ናቸው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ያለበት እዳ 36.6 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ


የኢትዮጵያ መንግስት እስከ ፈረንጆች አቆጣጠር 2015 ዓም ማጠናቀቂያ ድረስ ያለበት አጠቃላይ እዳ 36.6 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጠ።
ይኸው የሃገሪቱ የእዳ መጠን ከአጠቃላይ ሃገራዊ ምርት ጋር ሲነጻጸር ወደ 55 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ መንግስት ከሚያጸድቀው በጀት ውስጥ ለእዳ ክፍያ የሚመደበው ገንዘብ እየጨመረ መምጣቱ ታውቋል።
ለ2009 ዓም ከተያዘው 274 ቢሊዮን ብር በጀት መካከል መንግስት ወደ 14 ቢሊዮን ለእዳ ክፍያ መመደቡ ይታወሳል።
እንደፈረንጆቹ አቆጣጠር በ 2014/2015 ዓም የኢትዮጵያ አጠቃላይ በጀት ወደ 19 ቢሊዮን ዶላር ደርሶ የነበረ ሲሆን፣ ብድሩ በከፍተኛ ሁኔታ ጭማሪን በማሳየት በአሁኑ ወቅት 36.3 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን የገንዘብና የኢኮኖሚ ሚኒስቴር መረጃን ዋቢ በማድረግ ዘግበዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ እዳ መጠን ብቻ ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ መሆኑንና የእዳ መጠኑ የሃገሪቱ አጠቃላይ አመታዊ ምርት 30 በመቶ እንደሚሸፍን ታውቋል።
ለብድር የሚከፈለው የወሊድ መጠን ከፍተኛ መሆኑን የገልጹት የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች በበኩላቸው የሃገሪቱ አጠቃላይ እዳ እየጨመረ መምጣት በኢኮኖሚ እድገቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖን ማሳደሩን አስረድተዋል።
በተያዘው የ2008 አም ብቻ መንግስት ከአለም ባንክ የተበደረው እዳ 1.8 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ የቻይና መንግስትን ጨምሮ የተለያዩ አበዳሪ አካላት ከፍተኛ ገንዘብ በብድር ማቅረባቸው ታውቋል።
የአለም ባንክ በተያዘው በጀት አመት ለኢትዮጵያ ያበደረው ገንዘብ ከዚህ በፊት ከነበሩ ብድሮች ጋር ሲነጻጸር በመጠን ከፍተኛው ሆኖ ተመዝቧል።
ሃገሪቱ የምትበደረው ገንዘብ በመጨመር ላይ ቢሆንም ከውጭ ንግድ የሚገኘው የውጭ ምንዛሪና ክምችትን ግን እየቀነሰ መምጣቱን የንግድ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ መንግስት ያለበት የእዳ ክምችት እስከ 30 አመት በሚደርስ ጊዜ የሚጠናቀቅ በመሆኑ ሃገሪቱ በወለድ የምትከፍለው ገዘብ መጠን ከፍተኛ መሆኑ ይነገራል።

Sunday, June 12, 2016

የአባይ ወልዱ የአውስትራልያ ጉብኝት እና የወልቃይቶች አቀባበል ።

ዜና አባይ ወልዱ
አዊስትራሊያ ጉብኝት ለማድረግ ከገቡ በሆላ በወልቃይት ተወላጆችና በኢትዩጽያዊኖች ከባድ ተቃዉሞ ገጠማቸዉ
ሜልቦረን በተባለዉ ከተማ ስብሰባ ለመሳተፍ አስበዉ በተቃዉሙ አደራሹ ተዘግቶ መግባት አልቻሉም 
አባይ ወልዱ የትግራይ ርእሰ መስተዳደር ፕሪዚዳንት ሲሆኑ ሰሞኑን የወልቃይት አማራ ብሄር ጥያቄን ለማፈን
በመሲህ ሃይማኖት መሪወች ህዝቡን ሲያሰቃዮ የሰነበቱ ሲሆን ድካማቸዉ ሳይሳካ ቀርቶል እነሆ በዛሪዉ እለት
ማለትም በ5/10/08 አዉስትራሊያ ሚልቦርን ከተማ በወልቃይት ተወላጆች ተቃዉሞ ቁም ስቅላቸዉን እያዮ ነዉ
ወልቃይቶች በግፈኛዉ የትግራይ ቡድን ግፍ ከተሰደዱት በአዉስታራሊያ በርከት ያሉት ይኖራሉ
ወልቃይቶች ባገር ዉስጥ በዉጭ ሃገር እንደዘንድሮ ለማንነታቸዉ ቆርጠዉ ተነስተዉ አያዉቁም
ፖለቲካ ልይነት በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከቀረ እነሆ ከ2 አመት በላ ይ አስቆጠሩ ማንነት ከማንም በላይ ነዉ
ማንነቱ ያልተረጋገጠ ህዝብ ባህር ላይ እንዳለ ኩበት ነዉ
የአዉስትራሊያዉን ቪዲዮ እንደደረሰኝ ፖስት አደርጋለዉ
አባይ ወልዱ ከወልቃይት ጫንቃ እስካልወረደ ተቃዉሞችን በር ዉስጥም በዉጭ ሃ ሃገር ይቀጥላል !!
ድል ለወልቃይት አማራወች !!!

Saturday, June 11, 2016

ሰበር መረጃ . . በአሁኑ ወቅት የወያኔ ጀሌዎች የበርሊንን ስብሰባ ለማበላሸት ተቃዉሞ እያደረጉ ይገኛሉ!!


የብዙሃኖች ብሶት! የብዙሃኖች እንባ ለእነርሱ ምናቸዉም ነዉ! ኢትዮጵያ ልጆቿን በትና የጥቂቶች በሆነችበት በዚህ በመጨረሻዉ ወቅት ላይ የወያኔ ደጋፊ ነን ያሉ ጥቂቶች እየጮሁ ይገኛሉ! የእኛ ደም ደግሞ እንደ አቤል ደም በኢትዮጵያና በመላዉ አለም ላይ በእነርሱ እጅ ላይ ሆኖ ይጮሃል! ድሉ ወደፊት እየተስገመገመ ሲመጣ ይህን መሰል ጩኽት በየስፍራዉ እንደሚያስተጋባ የሚታመን ነዉና በጀርመን የምትገኙ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የወያኔና የወያኔያዊያንን ብድራት ከመክፈል አንጻር ስብሰባዉን ከዳር ለማሳካትና እነዚህን የወያኔ የደም ልጆች አንገት ለማስደፋት በተያያዛችሁት ሰላማዊ የተቃዉሞ መንገድ በርቱ! ወደፊት!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
ጉድሽ ወያኔ
Gudish Weyane's photo.
Gudish Weyane's photo.Gudish Weyane's photo.Gudish Weyane's photo.

Friday, June 10, 2016

ሰበር መረጃ.. በሶማሌያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደኍላ እንዲያፈገፍጉ ትእዛዝ ተላለፈላቸው!!


በተለይ በአሚሶም ዉስጥ ሀልጋን እየተባለ በሚጠራዉ ስፍራ የኢትዮጵያ ወታደሮች የሚቆጣጠሩት ምድብ በአል ሸባብ አጥፍቶ ጠፊ ሐይሎች መመታቱን ለመበቀል የተንቀሳቀሰ የሻለቃ ምሪት ሐይል ክፉኛ መጠቃቱን ተከትሎ ከኮረኔል የማነ በተላለፈ መመሪያ መሰረት የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ኍላ አፈግፈገዋል።
ድንገተኛዉን አደጋ ተንተርሶ በቦምብና በጥይት ጥቃት የፈጸመዉ አልሸባብ በሶማሌያ ሰራዊት እንዲሁም በአሚሶም ( በአፍሪካ ህብረቱ ) ጥምር ላይ ከፍተኛ አደጋ ማድረሱን ከለፈፈ ወዲህ ትንቅንቅ የገጠመዉ የኢትዮጵያ ወታደር በሶማሌያ ሴቶች ሳይቀር ከፍተኛ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን..
በሶማሌያ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ወታደር በየቀኑ እየረገፍፈ ከመሆኑ ባሻገር በዚህ ድንገተኛ ጥቃት ብቻ ከ74 በላይ ሲቆስሉ 40 በላይ መሞታቸዉንና ተከታትሎ ለማጥቃት በተደረገ ግብ ግብ ቁጥራቸዉ በዉል ያልታወቀ የኢትዮጵያ ልጆች ተሰዉተዋል ቆስለዋል አሁንም እየተሰዉ እየቆሰሉ ይገኛሉ።
በዚህ ዉጊያ ላይ የሶማሌያ ሴቶች አል ሸባብን በመደገፍ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )
Gudish Weyane's photo.

Thursday, June 9, 2016

የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ወደ $6.5 million US dollar ቅጣት እንዲከፍል ተበየነበት፥


የወያኔ ባለሥልጣናት የቦንድ ሽያጭ በሚል ሕገወጥ መንገድ በኢትዮጵያ መብራት ኃይል ስም ገንዘብ ለመሰብሰብ በአሜሪካ ከ 83 ዓመት በላይ የኖረውን የኢንቨስትመንት ሕግ በመጣሳቸው የቀረበባቸውን ክስ ተከትሎ የደረሱበት ስምምነት እንደሆነ ተገልጿል፥
የቆጥ ዓወርድ ብላ የብብቷን ጣለች ይሉሃል እሄ ነው!
SEC: Ethiopia’s Electric Utility Sold Unregistered Bonds In U.S.
The Securities and Exchange Commission today announced that Ethiopia’s electric utility has agreed to pay nearly $6.5 million to settle charges that it violated U.S. securities laws by failing to register bonds it offered and sold to U.S residents of Ethiopian descent. According to the SEC’s order instituting a settled administrative proceeding: Ethiopian Electric Power (EEP) conducted the unregistered bond offering to help finance the construction of a hydroelectric dam on the Abay River in Ethiopia. EEP held a series of public road shows in major cities across the U.S. and marketed the bonds on the website of the U.S. Embassy of Ethiopia as well as through radio and television advertising aimed at Ethiopians living in the U.S. EEP raised approximately $5.8 million from more than 3,100 U.S. residents from 2011 to 2014 without ever registering the bond offering with the SEC. “Foreign governments are welcome to raise money in the U.S. capital markets so long as they comply with the federal securities laws, including registration provisions designed to ensure that investors receive important information about prospective investments,” said Stephen L. Cohen, Associate Director of the SEC’s Division of Enforcement. “This settlement ensures that investors get all of their money back plus interest.” The SEC’s order finds that EEP violated Sections 5(a) and 5(c) of the Securities Act of 1933. EEP admitted the registration violations and agreed to pay $5,847,804 in disgorgement and $601,050.87 in prejudgment interest. The distribution of money back to investors is subject to the SEC’s review and approval. Investors seeking more information should contact the administrator of the distribution, Gilardi & Co. LLC, at 844­851­ 4591. The SEC’s investigation was conducted by Carolyn Kurr and Daniel Rubenstein and state

ከ10,000 በላይ መብታችን ተደፈረ ያሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ነዋሪዎች ቤተመንግስት ፊት ለፊት ድምጻቸውን ሲያሰሙ ዋሉ።


በን/ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ቀርሳና ኮንቶማ 30 ሽ ህዝብ የምኖርበት ሰፋር ለማፍርስ ያቀዱትን የቀበሌውን እቅድ ለመቃውም 4 ክሎ በምገኘው ቤተመንግስት ፊት ለፊት የተሰበሰቡት ከ10000 በላይ ሰዎች  በመሰብሰብ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል።
በኣራት ኪሎ ቤተመንግስት ፊትለፊት ድምጻቸውን ያሰሙ የተገፉ ህዝቦች የተሰጣቸው መልስ መድረክ እንፋጥራለን ወደ ሰፋራችሁ ሂዱ ብሎ ሸኝቶዋል ህዝቡ ግን መበተን አለፋለገም ከ4 ክሎ እስከ ሳሪስ በእግሩ እየሄደ ተቃውሞውን እያሰሙ ቆይተዋል በዋላ በፌደራል ፖሊሶች ሊበተኑ ችለዋል

መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.
መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.መቅዲ የአዴሃን ፍሬ's photo.

ግፍ አንገፍግፎቸው ከ ወያኔ ጋር ትንቅንቅ ለፈጠሩ አብዮተኞች ሁሉ !


ለ25 አመት በሁዋላ ያንቀላፉት አንበሶቹ ጀግኖቹ የዳባት ህዝብ የማይረሳ ታሪክ ሰሩ። ወደ ትግራይ ክልል ተጭኖ ሊሄድ የነበረን ትራንስፈርመር በወጣቱ ሀይል ቀርቷል ጭኖት የነበረዉ መኪና በእሳት አጋይቷል የመንግስት ተቋማት የመለስ ፖርክ የሚል ታፔላ ተገንጥሏል ። መስታዉቶች ተሰባብረዋል ካቢኔዎች የገቡበት ጠፍቷል ህዝቡ ድል ተቀናጅቷል ጎማዎች አስፋልት ላይ ይነዳሉ ይጨሳሉ ህዝቡ አደባባይ በመውጣት ተቋውሞውን እየገለፀ ነው ብዙ ፎቶዎች እና ቪዶዎች እየተለቀቁ ነው ዳባት ,,,,, አምቦ እና ምስራቅ ሐረርጌ መሰላ ,,,, የዳባት ከተማ በአብዮተኞቹ ወጣቶች ስር ወድቃላች ።
የወያኔ ግፍ እና በደል ያሰለቸው የደባት ህዝብ ከ ኦሮሚያ አብዮተኞች ትምህርት ቀስሞል አደባባይ መውጣት እና መብትን ማሰከበር ጀምረዋል ። በወያኔ ግፍ እና በደል እየማቀቅ ያለው የአማራ የዳባት ጀግኖችን የአርበኞችን ኮቴ ተከትሎ የ ኦሮሚያ አብዮተኞችን ወኔ ሰንቆ ለነፃነቱ እና ለመብቱ መታገል አለበት እላለሁ ።

Tuesday, June 7, 2016

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ መከላከል አትችሉም ተባሉ


የካቲት 4/2008 ዓ.ም ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል በዋለው ችሎት እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ( ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ እየሩሳሌም ተስፋው፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ) አቃቢ ህግ ያቀረበባቸውን ክስ በሰነድና በአንድ የሰው ምስክር ማስረጃዎች አስረድቷል በሚል ተከሳሾች መከላከል ይገባቸዋል ሲል ፍርድ ቤቱ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎም መከላከያ ማስረጃዎች ያቀርቡ ከሆነ በሚል ፍርድ ቤቱ ጠይቆ፣ ተከሳሾች 200 የሰው ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃዎች በጋራ እንደሚያቀርቡ አሳውቀው ነበር፡፡ ከዛ በኋላ በነበሩ ቀጠሮዎችም ምስክሮቻቸውን በዝርዝር ያስገቡ ሲሆን ከዛሬ ግንቦት 30 እስከ ሰኔ 8 , 2008 ድረስ ምስክሮቻቸውን እንዲያሰሙ ቀጠሮ ተሰጥቷቸው የነበረ ቢሆንም የቀጠሯቸው ቀን ሳይደርስ ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርበው ጭብጥ እንዲያሲዙ ተጠይቀዋል። እነሱም የምስክርነት ጭብጥ ምስክሮች መሃላ ሳይፈፅሙ መያዝ እንደሌለበት ለፍቤቱ አስረድተው ውሳኔውን ለመስማት ለዛሬ ተቀጥረው ነበር።
የዛሬው ውሳኔ ግን በጣም የሚደንቅ ነው። አራት ወር ሙሉ ፍርድ ቤቱ ሲሰጥ የነበረውን ትእዛዝ ይቃረናል። “መከላከያ ምስክር ማሰማት የለባችሁም ስለዚህ ለፍርድ ብይን ሃምሌ 13, 2008 ቅረቡ” የሚል ውሳኔ አስተላልፋለች ዳኛዋ።
Mahlet Fantahun's photo.

Sunday, June 5, 2016

ለነፃነታችን መክፈል የሚገባንን መክፈል አለብን

ለነፃነታችን መክፈል የሚገባንን መክፈል አለብን። በረሃ ላይ ያሉት አርበኞች ከገንዘብ በላይ ውድ ህይወታችን ነው ለዚህ ትግል የሰጡት! ይህ የህይወት መሰዋዕትነት ቀላል አይደለም። ትግሉ እስከ ነፃነት መደገፍ አለብን!!
ነፃነት ዋጋ ያስከፍላል!!
ድል ለኢትዮጵያዊነት!!!                 ትናንት በኖርዌይ አርበኞች ግንቦት 7 የተሳካ የገቢማሰባሰቢያ ዝግጅት አድርጎ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል:: በዚህ ስብሰባ ላይ የተገኙት የንቅናቄው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ያደረጉትን ንግግር ጌታቸው በቀለ እንደሚከተለው ጨምቆ አሰናድቶታል::
መድረኩን እና አድማጫቸውን ለሰዓታት በጉጉት ወጥረው የመያዙ አቅም ያላቸው ድምፀ ጎርናናው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ንግግራቸውን የጀመሩት ወደ ኦስሎ ከመጡ በኃላ ወዲያው ያደረጉት ከኖርዌይ ባለስልጣናት ጋር በኖርዌይ ስለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ መነጋገራቸውን እና ለኖርዌዮች ሊረዱት ይችላሉ ባሉት መንገድ ስለ ኢትዮጵያ ችግር ያስረዱበትን መንገድ አብራርተዋል።በመቀጠል የንግግራቸው ዋና ፍሬ ሃሳብ ስለነበረው የኢትይጵያን የአሁኑን የወያኔ ስርዓት ከፈረሰው የደቡብ አፍሪካ የዘር-መድሎ ስርዓት ጋር ያለውን ተመሳሳይነት፣የባሰ የሆነበትን መንገድ እና የትግል ስልቶቹን ዝምድና በሚገባ አብራርተዋል።
የደቡብ አፍሪካ የፈረሰው የዘር መስሎ ሥርዓት እና የወያኔ ስርዓት አንድነት እና ልዩነት
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የደቡብ አፍሪካን የዘር መድሎ ስርዓት የሚመሳሰልባቸውን ሁለቱ የስልት መንገዶች እንዲህ አብራርተዋል።
1ኛ/ የስነ-ልብና ጦርነት በብዙሃኑ ላይ ማድረግ
ነጮች ጥቂቶች ነበሩ።ታድያ እንዴት ብዙሃኑን ጥቁሮች እረግጠው ገዙ? ብለው ከጠየቁ በኃላ መልሱ የነጮች በጥቁሮች ላይ ያደረጉት የስነ-ልቦና ጦርነት አንዱ መሆኑን ሲያብራሩ ጥቁሮችን መጀመርያ ያደረጉት ጥቁሮች እኔ ለነፃነት ብቁ ነኝ እንዴ ? ብለው እራሳቸውን እንዲጠይቁ እና አለመሆናቸውን እንዲያስቡ የተደረገ የስነ-ልቦና ተፅኖ መኖሩን አብራርተው በተመሳሳይ ደረጃ ወያኔ በሕዝቡ ላይ ለነፃነት ብቁ እንዳልሆነ የረቀቀ የስነ-ልቦና ዘመቻ እንደሚያደርጉ አብራርተዋል።
2ኛ/ በጎሳ መከፋፈል
በደቡብ አፍሪካ ዘረኛው መንግስት አንዱ የተጠቀመበት መንገድ እራሳቸው ጥቁሮችን በጎሳ መከፋፈል እርስ በርስ እንዲጋጩ ማድረግ ነበር።በተመሳሳይ መንገድ ወያኔም እየሰራበት እንደሚገኝ ገልጠው የደቡብ አፍሪካ ትግልም እነኝህን ችግሮች አስታኮ ትግሉን በሶስት መንገዶች መቅረፁን አብራርተዋል።
የደቡብ አፍሪካ የነፃነት ትግል ሶስቱ የትግል መንገዶች
ፕሮፌሰር ብርሃኑ የደቡብ አፍሪካ ትግል የተከተላቸው መንገዶች ሶስት እንደነበሩ አብራርተዋል። እነርሱም:
ሕዝባዊ እምቢተኝነት በአገር ውስጥ፣
ሕዝባዊ እምቢተኝነት በውጭ አገሮች እና
በማንዴላ የሚመራው የመሬት ላይ የትጥቅ ትግል የሚሉ ነበሩ።
የደቡብ አፍሪካ ትግል ከላይ የተጠቀሱትን መንገዶች ይያዝ እንጂ የአገር ውስጡ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ግቦቹ ሁለት ነበሩ። እነርሱም መጪዋ ደቡብ አፍሪካ በዜግነት ላይ የተመሰረተች ትሆናለች የሚል እና አንድ ሰው አንድ ድምፅ ይኖረዋል የሚሉ ነበሩ። የውጭው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በተለይ አለምን ያነቃነቀ እና ዋና ትኩረቱ በዓለም ላይ ያሉ ታላላቅ ኩባንያዎች በደቡብ አፍሪካ ኢንቨስት በማድረግ የዘር-መድሎ ስርዓቱን እንዳይደግፉ ማድረግ ነበር። ሆኖም ግን ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ይህንን ሁሉ በደል እያዩ ደቡብ አፍሪካ ላይ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ያፈሱ ነበር። ሶስተኛው የትጥቅ ትግሉ ከጎረቤት አገሮች በመነሳት የደቡብ አፍሪካን ዘረኛ መንግስት ሰላም የመንሳት አላማ ነበረው። ይህ ትግል በተለይ በደፈጣ ውግያ የደቡብ አፍሪካውን ስርዓት ሰላም የነሳ እና ከጎረቤት አገራቱ ጋር ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ነበር።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ የሶስቱን የደቡብ አፍሪካ የትግል ስልት ካነሱ በኃላ ከሶስቱ የትኛው የተሻለ ስልት ነበር? የትኛውስ የበለጠ አስተዋፅኦ አደረገ? በማለት ከጠየቁ በኃላ መልሱን ሲመልሱ አንዳቸው ከአንዳቸው ይበልጣሉም ያንሳሉም ማለት እንደማይቻል አብራሩ። ሶስቱም እርስ በርስ ተደጋግፈው ነው ውጤት ያመጡት።በውጭ ያለውን ድጋፍ በማስቆም የአገር ውስጡን እምቢተኝነት መደገፍ ተችሏል።በትጥቅ ትግሉ እረፍት ነሺነትም ለድል መቃረብ ተችሏል በማለት የደቡብ አፍሪካን ሁኔታ ከገለጡ በኃላ ከእኛ ጋር ያለውን ልዩነት እና አንድነት እንዲህ አብራርተዋል።
የወያኔ ስርዓት እና የደቡብ አፍሪካ የዘር መድሎ ስርዓት ተመሳሳይነት
የወያኔ ስርዓት የደቡብ አፍሪካው ስርዓት ያለው አንድነት ሁለቱም መሰረታቸው በዘር ላይ የተመሰረተ መሆኑ፣በምጣኔ ሀብት፣ፖለቲካውን እና ያዩትን ሁሉ ለመቀራመት ያላቸው ፍላጎት እና በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ግድያ ፣እስር በዋነኛነት ይገለጣል።በእዚህ ተመሳሳይ ለትግሉ በእኛ በአርበኞች ግንቦት 7 በኩል የቀየስነው የትግል ስልትም ሶስቱን ማለትም ሕዝባዊ እምቢተኝነት በአገር ውስጥ፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነት በውጭ አገር እና መሬት ላይ የሚደረግ የትጥቅ ትግል የሚሉት ናቸው። ሶስቱም አንዳቸው ከአንዳቸው ተደጋግፈው የሚሄዱ መሆናቸውን በሰፊው አብራርተዋል።
የደቡብ አፍሪካ የዘር መድሎ ስርዓት ከወያኔ የተሻለባቸው መንገዶች
ፕሮፌሰር ብርሃኑ የደቡብ አፍሪካ ዘረኛ ስርዓት ከወያኔ የሚለይባቸው እና የተሻለባቸው መንገዶችን እንደሚከተለው አብራርተዋል።
ሀ/ በደቡብ አፍሪካ ስርዓቱ አፓርታይድን በሕግነት አውጥቶ ስለ አወጣው ሕግ ይከራከራል እንጂ ያወጣውን ሕግ ሰርዞ ወይንም የሌለ ሕግ ትጠቅሶ አይከራከርም ነበር። በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ በሕግ ተደንግጎ ነበር። ስለሆነም ስርዓቱ የቆመው ላወጣው ሕግ ነበር።ወያኔ ግን ያወጣውን ህገ መንግስት በመጣስ ሕግ የሚያሰቃይ ነው
ለ/ የደቡብ አፍሪካ ስርዓት ስለ ውደፊቷ ደቡብ አፍሪካ ይወያይ ነበር።ቢያንስ ወደፊት የጎደለውን ማሟላት ያለባት ደቡብ አፍሪካ መኖር አለባት በማለት በእስር ቤት ከሚገኙት ማንዴላ ጋር ማቆምያ የሌለው ግን እስር ቤት እየሄደ ይወያይ ነበር።ይህ ማለት ስለተባበረች ደቡብ አፍሪካ መጨነቅ ነበር። የወያኔን ስርዓት ብትመለከቱ ስለ ወደፊቷ ኢትዮጵያ የሚባል ራእይ የላቸውም።ስለመተባበር፣ህብረት ወዘተ ምንም የማይጨነቁ ናቸው።
ሐ/ በደቡብ አፍሪካ የፍትህ ስርዓቱ ላይ መንግስት እጁን አያስገባም። ይልቁንም መንግስት ብዙ ጊዜ የተረታባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ።ይህ ብቻ አይደለም የአፓርታይድ ስርዓት ከበርካታ የሰራተኛ ማኅበራት ጋር የገጠሙት አመፆች የሰራተኛ ማኅበራቱ የነበረውን የሕግ ስርዓት ተንተርሰው ስለሚንቀሳቀሱ ነው። የወያኔ ስርዓት ስትመለከቱ የፍትህ ስርዓቱን በሙሉ ደምስሶ በእራሱ የያዘ እና መቀለጃ ያደረገ ነው።ተመልከቱ! ከደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ስርዓትም ምን ያህል የከፋ ስርዓት ላይ እንደሆንን።
መ/ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብን ስንመለከት በአፓርታይድ ዘመን ዓለም ድምፁን ያሰማው ለምሳሌ ትልቁ ከሚባለው የሻርፕቪል እልቂት ላይ የሞተው የሰው ቁጥር 64 ሰው ነበር።በእዚህ ብዙ አገሮች ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቆሙ ሆነዋል።እኛ ጋር በ1997 ዓም ብቻ እራሳቸው እንዳመኑት 197 ሰው ሲገደል ዓለም ለእኛ አይጮህም።ጋምቤላ ከ400 ሰው በላይ ሲያልቅ ዓለም አይናገረም። በቅርቡ በኦሮሞ ወንድሞቻችን ላይ ከ500 በላይ ሲገደሉ ከ30ሺህ በላይ እስር ቤት ስታጎሩ ዓለም እንዳልሰማ ዝም ብሏል። ካሉ በኃላ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በመቀጠል እንዲህ አሉ:
”ስለሆነም አሁን ዓለም ተቀይሯል።ማንም ፈረንጅ ለእኛ ችግር ከእኛ በላይ ማንም መፍትሄ ሊያመጣ አይችልም።ነፃነት አጥተህ መብላት መጠጣትህ ሰው አያደርግህም።” ብለዋል።በመጨረሻም ስለ አርበኞች ግንቦት 7 መጪ የትግል ሂደት ሲያስረዱ ይህንን ብለዋል:
መጪው ትግላችን ትግሉን በድንበር አካባቢ ማቆየት ሳይሆን ወያኔ በር ድረስ ማድረስ ነው።እዚህም አብዛኛውን የወያኔ ኃይል ለትግሉ ማሰለፍ ነው።ይህ ትግል ወያኔዎችን እራሳቸውን አሳምኖ ለሕዝብ እንዲቆሙ ማድረግ መቻል አለበት። እናንተም ስታገኙዋቸው ደግግማችሁ ጥቂቶች ስለሚሰሩት አስረዷቸው። በነገራችን ላይ የኢትዮጵያ ሰራዊት ጋር እኛ ፀብ የለንም።የእኛ አላማ እንደ ወያኔ ተቋማትን ማፍረስ አይደለም። ያሉትን ጠብቀን የተሻሉ መገንባት ነው።እኛ ከድል በኃላ አሁን ያለውን ሰራዊት የምናፈርስበት ምንም ምክንያት የለም ብለዋል።














Ag7 Fundraising in Oslo Sweden