Thursday, May 5, 2016

በቬጋስ የትግራይ ተወላጆች ብቻ የተሰብሰቡበት ስብሰባ ተበጠበጠ።


ከቬጋስ አሁን የደረሰኝ መልእክት
ሰሞኑን የብአዴንና የአማራ ክልል ባለስልጣናት በአሜሪካና አውሮፖ ተሰማርተዋል። የትግራይ ተወላጆች የሚበዙባቸውን ስለአማራው ክልል የሚመክሩባቸው ስብሰባቸውን እያደረጉ ነው። በአብዛኛው በተቃውሞ ከሽፈዋል። ስለአማራው ትግራዩ ቢመለከተው አይገርምም። አማራዎች እንዳይሳተፉ መደረጉ ግን ግራ የሚያጋባ ነው።
ቬጋስ በዚህን ሰዓት ተመሳሳይ ስብሰባ ተጠርቶ እየተካሄደ ነው። የቬጋሱ የሚለየው በስብሰባው የተገኙት በሙሉ የትግራይ ተወላጆች ናቸው። ሰብሳቢዎቹ የብአዴን ከፍተኛ ባለስልጣንና የአማራ ልማት ማህበር ሊቀመንበር ናቸው። ሌሎች እንዳይገቡ በር ላይ የተከለከለ ነው። በዚህም ግጭት ተፈጥሮ የቬጋስ ፖሊስ ደርሶ በአስለቃሽ ጢስ ለመበተን እየሞከረ ነው። አሁንም ፍጥጫው እንዳለ ነው

No comments:

Post a Comment