Tuesday, May 3, 2016

ከአውሮፓ ኢትዮጵያ ኑሮውን ለማድረግ የገባው ወጣት በሳንጃ ተወግቶ ተገደለ


በፈትያ አንዋር
ዓመት በዓል ከመድረሱ ሳምንት በፊት ጀምሮ የተለያዩ ውክቢያዎች፣ ፈንጠዚያዎች እንዲሁም ደስታና ሳቅ፣ በሌላ ጎኑ ደግሞ ሀዘንም ሊኖር እንደሚችል እሙን ነው፡፡
ባሳለፍነው የፋሲካ በዓል ዋዜማም በጣም አስደንጋጭ ነገር ተፈጥሯል፡፡ መቼም ሰው ነንና በበዓል ዋዜማ ደስታችንን ለመግለፅ ወደተለያዩ መዝናኛ ቦታዎች ማምራታችን የማይቀር ነው፡፡ በዋዜማው በአዲስ አበባ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ውስጥ ሁለት የዛው አካባቢው ነዋሪዎች ሊዝናኑ በወጡበት ባልታሰበ ፀብ በሳንጃ የአንደኛው ሰው ሕይወት ሲያልፍ ሌላኛው ደግሞ ሳንባው ተወግቶ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምንና ላይ ይገኛል ፡፡

No comments:

Post a Comment