Tuesday, May 31, 2016

እነ ብርሀኑ ተ/ያሬድ ያለቀጠሮአቸው ተገደው ፍርድ ቤት ቀረቡ


ፍርድ ቤቱ የተክሳሽኦችን የመክላክያ ምስክሮች በምን ጭብጥ ላይ እንደሚያስመሰክሩ ከምስክሮቹ ቀጠሮ አስቀድሞ እንዲገለፅ ጠይቃል።
–ተከሳሾቹ ፍርድ ቤቱ እና ማረሚያ ቤት ህገወጥ ጫናና ወከባ እየፈጠሩብን ነው ብለዋል የክስ መዝገባቸው በከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት
በመታየት ላይ የሚገኘው 4 ተከሳሾች ብርሀኑ ተ/ያሬድ ፤እየሩሳሌም ተስፋው፤ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ
ብይን በሰጠባቸው ጉዳአዮእ ላይ የመከላከያ ምስክር ለማቅረብ ከግንቦት 30-ሰኔ 8 ክትሮ ተይዞላቸው የነበረ ቢሆንም ዛሬ ግንቦት 23 ቀን ያለቀጠሮዋቸው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተደርጋል ተከሳሾቹ ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሌላቸው ለማረሚያ ቤቱ ሀላፊዎች የገለፁ ቢሆንም በማረሚያ ቤቱ የጥበቃ ሃላፊዎች
ወከባና ግፍተራ እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችላል። ተከሳሾቹ ፍርድ ቤት ከቀረቡም በኃላም ለፍርድ ቤቱ ይህንን ያስረዱ ሲሆን የፍርድ ቤቱም ዳኛም “ዛሬ ቀጠሮ ባይኖራችሁም ፍርድ ቤቱ ማጣራት ያለበት ጉዳይ ስላለ ነው የጠራናችሁ”በማለት የተከሳሾቹ መከላከያ ምስክሮች የሚመሰክሩበትን ጭብጥ ተከሳሾቹ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ
እንዲያስረዱ ጠይቀዋል ተከሳሾቹም ምስክሮቻቸው የሚመሰክሩበት ጭብጥ ምስክርነት በሚሰጥበት እለት እንጂ ምስክሮቹ ከመቅረባቸው አስቀድሞ ለፍርድ ቤቱ የማሳወቅ ህጋዊ ግዴታ የሌለባቸው መሆኑን የገለፀ ሲሆን ዛሬ በፍርድ ቤቱ እየተጠየቁ ያለው ቅድመ ሁኔታ ግን ህጋዊ መሰረት የሌለው እና ፍርድ ቤቱም የሌሎች የገዢው ፓርቲ የአፈና መዋቅርት ተፅእኖ እንዳረፈበት የሚያሳይ ነው ብለዋል. ተከሳሾቹ አያይዘው እንደገለፁትም ለምስክሮች የተዘጋጀው መጥሪያ በፍርድ ቤቱ ዳኛ ተፈርሞ ለምስክሮቻቸው እንዲሰጥ ማረሚያ በት ለሚገኙ ተከሳሾች ከደረሳቸው በሀላ በድጋሚ“በፍርድ ቤት ትእዛዝ ነው” በሚል ምክንያት መጥሪያዎቹን
የተነጠቁ ሲሆን በማረሚያ ቤቱ ሀላፊዎች በኩልም መከላከያ ምስክሮቻቸውን በተመለከተ በተለይም የገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት ለምስክርነት ማስጠራታቸውን ተከትሎ ማስፈራርያና ወከባ እየደረሰባቸው ነው በመጨረሻም ተከሳሾቹ የምስክሮቻቸውን ጭብጥ ለፍርድ ቤቱ እንደማያሳውቁ በአፅንኦት የገለፁ ሲሆን የፍርድ ቤቱ ዳኛ “ከአነጋገራችሁ የምስክሮቹን ጭብጥ ለመረዳት ጭለናል በመሆኑም ይህኑኑ ጉዳይ መርምረን ለግንቦት 30-2008 ብይን እንሰጥበታለነረ “ በማለት ተከሳሾቹን በተጠቀሰው ቀን እንዲርቡ ትእዛዝ ሰጥተዋል።

28/05/2016 Ethiopian in Stockholm was to attend a fundraising gathering...

Monday, May 30, 2016

ዜና መረጃ… በረከት ስሞን አርበኞች ግንቦት 7 ያለዉ ዉስጣችን ነዉ ይላሉ!!


ወሎን ሰፈር ተሻግሮ ሩዋንዳ ሙልሙል ዳቦ አካባቢ ወደ ቦሌ በሚወስደዉ መንገድ በስተቀኝ ወደ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ይገኛል ከዩኒቨርሲቲዉ በተጓዳኙ በስተግራ ካለዉ ነጭ ህንጻ ላይ በደረጃ ቀስ እያልን ወደ 5ተና ፎቅ አመራን ከቢሮዉ በተያያዘ ቱሪዝም ኤጀንሲ ባጎራባች ሲኖር ከስሩ ደግሞ ሱፐር ማርኬት አለ በዋናነት ወደዛ የሄድንበት ምክንያት የበረከት ስሟን ቢሮ እዚያ እንደሚገኝ በደረሰን መረጃ መሰረት ነዉ።
ቢሮዉ እነደደረስን ጸሐፊዉን ለማግኘት ትንሽ ብንጠብቅም አግኝተን አናገርናት የበረከት ስሞን ቢሮ መሆኑን ካረጋገጥን በኍላ ትንሽ ጠብቁ ተብለን ተቀመጥን ከጥቂት ቆይታ ወዲህ በረከት በሁለት ሰዎች መካከል ሆኖ ከተፍ ሲል ተመለከትነዉ የመሰብሰቢያ ቢሮ በመሰለዉ ቢሮ ዉስጥ በአይኑ ሁላችንንም ገርበብ አድርጎን በአንገቱ ሰላምታ ሰጥቶን ወደ ዉስጥ ዘለቀ!
እኛም እዚያዉ መጠበቅ ጀመርን ከጥቂት ቆይታዎች በኍላ እቃ እንደረሳንና በሌላ ቀን እንደምንመለስ ለጸሐፊዋ ነግረን ተመልሰን ወጣን።
መኪናችን ዉስጥ ገብተን ወደተቀመጥንበት ሆቴል ገሰገስን ክፍላችን ዉስጥ እንደገባን መቀረጸ ድምጻችንን በቢሮዉ ዉስት ንደምን ለጥፈነዉ እንደወጣን እየተወያየን ተዝናናን!
ክትትላችንንም በመጠኑ በተለያዩ አካሎቻችን በማከናወን መግቢያ መዉጫቸዉን አጠናን ከ3 ቀናት በኍላ የተቀረጸዉን ድምጽ በእጃችን አስገባን መቅረጻችንም በጥቂቱ ይህን ይዟል።
_አቶ በረከት… አርበኞች ግንቦት 7 በየሐገሩ በየቦታዉ የተደራጀ ሐይል አለዉ ከእንግዲህ አ/ግንቦት 7 ልግባ መንገድ ልቀቁልኝ ወይም አሳልፉኝ አይልም ከእንግዲህ አ/ግንቦት 7 ገፍትሮንም አይገባም አ/ግንቦት 7 ያለዉ ዉስጣችን ነዉ! ከባዱ ስራ የሚሆነዉም ይህዉ ነዉ! የሚጠረጠሩ ግለሰቦች በሙሉ የመኖሪያና የመስሪያ ቦታቸዉ ድረስ እየተዞረ የፎቶና የተለያዩ ተጨባጭ መረጃዎች ይያዝ! ያለበለዚያ ምን እንደምንሰራ አይገባንም።
_አቶ ሳህረ የሚባል የብሄራዊ መረጃ ተወካይ…. በትክክል ብለዋል አቶ በረከት አባሎቻችን መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ነዉ የመጣነዉ እንዲሁም ከማህበራዊና ቱሪዝም ቢሮ ነዉ የመጣነዉ እያሉ ቤት ለቤት ሁሉ እየዞሩ ነዉ። ግን መረጃዎችን ለማግነት ይህ ብቻ በቂ ነዉ ብለን አናስብም።
በሌላኛዉ እለት እዚያዉ ቢሮ ተገኘንና አቶ በረከትን አነጋግረን ድምጸ መቅረጻችንን ካስቀመጥንበት አንስተን ወጣን እንግዲህ በአሁኑ ወቅት ወያኔ ይህዉ ነዉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
( ጉድሽ ወያኔ )

Saturday, May 28, 2016

Ethiopian in Stockholm was to attend a fundraising gathering about the Esat day

  • Ethiopian Satellit Television ESAT sixth year anniversary of service started date colorfully honored in Sweden the capital of Stockholm may 282016. From Amsterdam ESAT journalist Gelila Mekonen and Afework Agdaw top guest inattandance.
  • Program which was started by the religious father talk next come discussion about the day was and also stating the love and respect song for ESAT, Traditional dance and poetry competition was also near.
  • The main reason establish enthusiat ESAT is there is no any free media in Ethiopia. As a result , the society can not get any information. The dectator and racists Government purpusely preventing infomation from society. To eliminat this problem ESAT last 6 years work hard  vital information access to society this has high contributed  build democratic country, human right and low honored, based on race and corruption rule to become end so ESAT founded six year ago too fight at this level. http://video.ethsat.com/?p=25689
                                                                                                 

Friday, May 27, 2016

ሰበር መረጃ በኢቲዮ_ኤርትራ ድንበር ከፍተኛ ጦርነት በነፃነት ዓሎችና በወያኔ ወታደሮች ተካሄደ


74 ከአ/አ ከጎንደር ከሀረር ደቡብ ወዘተ የተሰባሰቡ ነፃነት የጠማቸዉ በምህንድስናና በጤና ድግሪ ያላቸዉ ወጣቶች በኢቲዮ_ኤርትራ ድንበር ከተማ ከትመዋል ወጣቶቹ ከመላዉ ኢ/ያ የተሰባሰቡት ቀጭን ቀጠሮ ይዘዉ ነዉ:: ማእከላዊነት ፈጥረዉ ሁሉም ሌሎች የተቀጣጠሯቸዉን ይጠባበቃሉ:: ከወጣቶች መሀል አንደኛዉ ስልኩ ቢዚ ሆኗል:: ቶሎ ቶሎ ያናግራል:: የሚያወራዉ ስልክ Unknown number ይላል:: ስልኩ ከኢትዮጵያ ዉጭ ነዉ::
”ሃሎ ሃሎ” ይላል ልጁም ተመሳሳይ መልስ ይመልሳል::
”ከርቀት እየተጠባበቃችሁ ተንቀሳቀሱ መንገድ ጀምሩ ስላችሁ ብቻ ወደተከዜ ሰሜን አቅጣጫ ኑ:: የሚመራችሁ ከጀርባዉ የኢትዮጵያ ባንዲራ የተለጠፈበት ወጣት ይመጣል:: እሱ ወደሚሄድበት ተከፋፍላችሁ ከ7 በማይበልጥ ስብስብ ተከተሉት:: አሁን ልጁ ይታያችሁዋል አደል? ጀምሩ!”
አለ የማይታወቀዉ ስልክ ይመጣል የተባለዉ መጣ:: 7 ሰባት እየሆኑ መከተል ጀመሩ:: ጫፍ ላይ ደርሰዋል:: በአካባቢዉ ዝር የሚል የለም:: የሚመራዉ ጠንከር ፈርጠም ያለዉ ወጣት ጃኬቱ ስር ታጥቋል:: ከመቅፅበት ቁም የሚል ከሁለት አቅጣጫ ከአንድ ጥይት ጋር ተሰማ:: የኢ/ያ መከላከያ 24ኛ ክ/ጦር ሻለቃ አባል ነበር:: ወዲያዉ ቁም ያለዉ ወታደር ተመቶ ወደቀ:: ማን እንደመታዉ አልታወቀም:: ወጣቶቹ ግራ ገባቸዉ:: ተኩስ ከየአቅጣጫዉ ይፈነዳል:: የኢ/ያ ወታደሮች በየቦታዉ ሲወዳድቁ ይታያል:: ጥይት ወደወጣቶቹ አልተተኮሰም::
”ማን ከማን ጋር ነዉ?” ሲል ከፊት የሚመራዉን ፈርጣማ ወጣት ከወጣቶቹ ሲደዋወል የነበረዉ ጠየቀ::
”አይዟችሁ ደርሰዋል:: እኛን የሚመሩን የነፃነት ሀይላችን ሰራዊት ሊያጠቁን ከመጣ ከወያኔ ወታደር ጋር ነዉ የገጠሙ:: ደርሰናል:: ቅርብ ናት የ5 ደቂቃ መንገድ ነዉ የቀረን ጀግኖቹ እየተፋለሙ ነዉ:: እኛ ሰላም ነን… ”…
(የቀጠለ) በርቱ ደርሰናል:: አሀን ያለንበት የኤርትራ ምድር ነዉ:: ቅድም ወንዙን ከመሻገራችን በፊት ያለዉ መሬት ነዉ የኢትዮጵያ:: ዉጊያዉ ያለዉ ከኢትዮጵያ መሬት ነዉ:: አንዱን ሻለቃ የ24ኛ ክፍለ ጦር እያርበደበዱት ያሉት ከ30 የማይበልጡ የነፃነት ጉዋዶቻችን ናቸዉ:: የዉስጥ አርበኞችም እያገዟቸዉ ነዉ:: ገዥ መሬት ስለያዙ ለማጥቃት አይቸገሩም:: ትርርርር ያለ ተኩስ የሚተኩሱት ወያኔወች ናቸዉ እዉር ድንብሱን ተስፋ በቆረጠ መልኩና እየተብከነከኑ ስለሚተኩሱ ድምፁ እንደዛ ነዉ በአንድ ቃታ ነዉ 30 ጥይት የሚጨርሱት:: በፍርሀት ሳያስቡት እኛን ለመብላት ብቻ ስለመጡ ሳያስቡት በገጠማቸዉ ጠንካራ ጡጫ ተደናብረዋል:: ብዙዉን ማጥቃትም መከላከልም አያደርጉም በተለይ እንደዛሬዉ ካላሰቡት:: ወደሀዋላ ነፋስ እየደበደቡ እየተኮሱ ነዉ እግሬ አዉጭኝ የሚሮጡት:: በመትረየስ ሽፋን ጣ….ጣ…ጣ…ጣጣጣ…ጣጣ የሚለዉ ተኩስ ድምፅ ደሞ የኛወቹ የነፃነት ሀይሎች ናቸዉ:: እያዩ ነዉ የሚሮጠዉን የሚቀልሙት:: የወያኔ ወታደር ነፃነት ሀይሎች መጡ ከተባለ ላብ በላብ ነዉ የሚሆኑ:: በፍርሀት ነዉ ቀድመዉ ነዉ የሚሞቱት:: የተማረኩ ወታደሮች የሚሉትም ይሄኑ ነዉ:: በነፃነት ሀይል ባህል ተኩሶ አደለም መሳት ያሰቡት ነጥብ ላይ አለማሳረፍ ያሳፍራል:: ታያላችሁ ማንም ሳይሰዋ ነዉ የሚመለሱት… ለማንኛዉም እኛ ወደካምፕ ተጠግተናል:: በሁለት ተሰለፉ 27 ሀያ ሰባት ሁኑ::” አለ መሪያቸዉ:: የነፃነት ታጋይ አባል:: ወዲያዉኑ የነፃነት ሀይሎች ከርቀት በተረጋጋ መንፈስ ሲመጡ ይታያሉ:: ፈርጣማዉ የነፃነት ሀይሎች አባል አጨበጨበ:: ”ይሄዉ ታጋዮቻችን ሁለት ሶስት ክላሽና መትረየስ እየተሸከሙ ከሄዱት 30 ተራብተዉ 55 ሆነዉ እየመጡ ነዉ:: የነፃነት ሀይል መሸነፍ አያዉቅም:: በተለይ እጅ መስጠት
ጠት አይታሰብም:: (የቀጠለ)…ብም:: ሁሉም በድል ተመልሰዋል:: እዛዉ ስለምንገናኝ እንድረስና አረፍ እንበል:: እንግዲህ ሀያ አምስቱ ተጨማሪወቹ የወያኔ የተማረኩትና የዉስጥ አርበኞች ናቸዉ ማለት ነዉ:: ቃኘዎችና የዉስጥ አርበኞቻችን ነበሩ:: የመሩት እነሱዉ ናቸዉ:: የዉጊያዉን ሁኔታ እስቲ ልጠይቅ…” ብሎ መገናኛዉን አወጣና ነካ:: ”ሀሎ ኦ7 ሃሎ ይሰማል ኦ7 ይሰማል:: ኦ74 ነኝ!” አለ:: ”ከዛኛዉ ማዶም ሀሎ ኦ74 ይሰማል ኦ7 ነኝ በሰላም ገባችሁ? እያየናችሁ
ነዉ:: እኛ በሰላም ተመልሰናል:: የተወሰነ ማርከናል ከ171 በላይ ሙትና ቁስለኛ ተመዝግቧል ከኛ 2 ጉዋዶች በመጠኑ ቆስለዋል:: ሁላችንም ጠመንጃወችና
ትጥቆችን ማርከናል:: የዛሬዉ በተለይ ከንጋጋቱ ያገኘነዉ ድል ልክ የለዉም:: ከባድ ጉዳት ነዉ ያደረስነዉ:: የዉስጥ አርበኞቻችንም ይዘናል:: የተሳካ ነዉ:: በቀን
16/09/2008 ቀንቶናል::” በሉ እዛዉ እንገናኝ ቻዉ ኦ74 ቻዉ ሞርኮ የሚቀበለን ደጀን ሀይል ደርሶልናል:: ሰላም ግቡ ደርሰናል::” ብለዉ ተሰነባበቱ::
በ16/09/2008 ሌሊት ጀምሮ ከመላዉ ኢትዮጵያ ተጠራርተዉ የመጡ ወጣቶችን ወደ ነፃነት ሀይሎች ለመቀላቀል የተደረገ ፍልሚያ በነፃነት ሀይሎች አሸናፊነት ከ171 በላይ የወያኔ ወታደር በመግደልና በማቁሰል የጦር መሳሪያም በመማረክ ነፃነት የጠማቸዉን ወጣቶች በሰላም እንዲቀላቀሉ በማስቻል ተጠናቀቀ::
ህሊና ፀረወያኔዋ
 

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ስላለው የዴሞክራሲ ችግር ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር እየተወያየሁ ነው

በኢትዮጵያ ባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የዴሞክራሲ ችግሮች ላይ ዝምታን መርጧል የሚል ትችል እየቀረበበት ያለው የአውሮፓ ህብረት በሃገሪቱ ያለውን ችግር በተለያዩ መድረኮችና ከባለስልጣናት ጭምር በመግለጽ ላይ መሆኑን አስታወቀ።
በቅርቡ በኢትዮጵያ ጉብኝትን ያደረጉና ከጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በሃገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የመከሩት የሃገሪቱ የፓርላማ አባላት “ትክክለኛ የሆነ አመራር በአፈና ላይ የተመሰረተ መሆን የለበትም” ሲሉ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በአካል ቅሬታቸውን መግለጻቸውንም ይፋ አድርገዋል።
በአውሮፓ ፓርላማ ካሉ የፖለቲካ ተወካዮች መካከል ዋነኛ የሆነው የሶሻሊስትና የዴሞክራቲክ ጥምር ፕሬዚደንት የሆኑት ጅያኔ ቲፔላ ህብረቱ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተመለከተ ዝምታን አለመምረጡና ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ እየተከታተለው እንደሆነ አዲስ ስታንዳርድ ከተሰኘ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል።
እንደሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ሁሉ በኢትዮጵያ ያለውም የልማት እንቅስቃሴ ከዴሞክራሲ ተለይቶ የሚታይ ጉዳይ አለመሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሽብርተናነትን ለመዋጋት በሚል በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ችላ ብሎታል ተብሎ ስለሚቀርቡ ቅሬታዎች የተጠየቁት ጂያኒ ቲፔላ በሃገሪቱ በመገናኛ ብዙሃን የፖለቲካ አመራሮች ላይ የተወሰዱ የእስር ድርጊቶችን በአደባባይ በማውገዝና ስጋታቸውን በመገለጽ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ለጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በተወያዩ ጊዜ ይሁንኑ ጉዳይ በአግባቡ ማስረዳታቸውንና ህብረቱ ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ይልቅ ለዴሞራሲ መከበር ቅድሚያ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
የአውሮፓ ፓርላማ ቡድን በቅርቡ በኢትዮጵያ ላይ ሊወሰዱ ስለሚገቡ ጉዳዮች የተጠየቁት የፓርላማ አባሉ፣ ህብረቱ ውሳኔውን ካስተላለፉ በኋላ የሚወሰዱ ለውጦችንንና እርምጃዎችን እየተከታተለ መሆኑን አክለው አስረድተዋል።
በኦሮሚያ ክልል የተፈጸመውን ግድያና የጅምላ እስራት ተከትሎ የአውሮፓ ፓርላማ በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ አስቸኳይ ጉባኤን በመጥራት የተለያዩ ውሳኔዎችን ማፅደቁ ይታወሳል።
በጸጥታ ሃይሎች የተገደሉ ሰዎች ድርጊት እንዲጣራ ጥያቄን ሲያቀርብ የቆየው ህብረቱ ከተቃውሞው ጋር በተገናኘ ለእስር የተዳረጉ የፖለቲካ አመራሮችና ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁም በማሳሰብ ላይ ነው።

Thursday, May 26, 2016

ጋዜጠኛ ጌታቸውን ከከሰሱበት ፍሬከርስኪ ክሶች መካከል የተወሰደ


“ተከሳሽ በሚጠቀምበት ማሀበራዊ ድህረ ገጽ በተለይም ፌስ ቡክ አድራሻዉን ተጠቅሞ በዉጭ አገር ከሚገኝ የሽብር ቡድኑ ግንቦት ሰባት አመራር እና አባል የሆነው ግርማ ካሳ ተብሎ የሚጠራ ግንኙነት በመፍጠር በሽብር ቡድኑ የተሰጠዉን ተልእኮ በማስፈጸም በቀን 27/2/2007 ዓ/ም፣ በ28/2/2007 ዓ/ም፣ በ10/6/2007 ዓ/ም፣ በ11/06/2007 ዓ/ም፣ በ18/06/2007 ዓ/ም፣ በ01/07/2007 ዓ/ም እየተገናኙ ስለ ግንቦት ሰባት እና አሸባሪ ተብለው የተከሰሱትን ቤተሰቦቻቸው እንዴት ሊደገፉ እንደሚችሉ የሚገልጽ የተለያዩ ይዘት ያላቸው መረጃዎች የተለዋወጡ በመሆኑ በዝርዝር ያደረጉት ንግግር በክሳችን በተጠቀሰው ማስረጃ የቀረበ በመሆኑ”…
ጋዜጠኛ ጌታቸውን ከከሰሱበት ፍሬከርስኪ ክሶች መካከል የተወሰደ ነው። የአንድነት ፓርቲ እውቅናዉን ከተነፈገ በኋላ የአንድነት ደጋፊዎችና ለሎች አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፣ የእስረኞች ኮሚቴ አቋቁመን፣ መጠነኛም ቢሆን የሕሊና እስረኞች ቤተሰቦችን (ኢኮኖሚካሊ ችግር ላይ ያሉትን) ለመደገፍ ጥረት ስናደርግ ነበር። በቂ ነበር? በቂ አልነበረም። ካደረገነው የበለጠ ማድረግ እንችል ነበር ? በሚገባ። ግን ትንሽም ብትሆን ከምንም ይሻላል።
አሁንም ያ ጥረት እየቀጠለ ነው። የአንድነት እስረኞችን ብቻ ሳይሆን፣ የመድረክ፣ የሰማያዊ፣ የመኢአድ፣ ጋዜጠኞና በዉሸት ክስ በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተከሰው የተፈረደባቸውንም ሳይቀር። የትም ድርጅት ይሁኑ ሁሉም የታሰሩት ለአገርና ለሕዝብ ነውና የሕሊና እስረኞች ናቸው። ጀግኖቻችን ናቸው።
በዚህ ረገድ የምናደርገው እንቅስቃሴን ነው እንግዲህ “ሽብርተኝነት” ተደርጎ ለክስ እያቀረበ ያለው። በዉሸት ክስ መከሰሳቸው ሳያንሳቸው፣ እስረኞችን ኢሰብዓዊ ጭካኔ እየፈጸሙ መደብደባቸው ሳያንሳቸው፣ የነርሱን ልጆች ለመዝናናት በፓሪስና በዱባይ እየላኩ የሌሎች እስረኞችን ልጆች ያስራቡት ሳያንሳቸው ፣ አሁን ደግሞ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ለእስረኞች ቤተሰቦች ድጋፍ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ “ሽብርተኝነት ነው” ይላሉ። ከዚህ የበለጠ ጭካኔ፣ ከዚህ የበለጠ አሪዮስነት ምን አለ ?
በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ አይምሮ አለን የምትሉ የኢሕአዴግ ደጋፊዎች እንድትጽፉና የምትደግፉት ድርጅት አመራሮች ላይ ግፊት እንድታደርጉ በአክብሮት እጠይቃለሁ። ይኸው 25 አመት ደፈናችሁ። ምንድን ነው እየሆናችሁ ያላችሁት። በጫካ ከነበረችሁበት ጊዜ ሁሉ የባሰ አዉሬዎች እየሆናችሁ ነው ? እንዴት ነው ሳንወድ በግዳችን፣ የምንቃወመዉን ደርጅት እንድነቀላቀል ነው እንዴ የምትፈልጉት? እኛ የግንቦት ሰባት አካሄድ አያዋጣም እያልን እየተከራከርን፣ መልሳችሁ እኛን ” የግንቦት ሰባት አመራር አባል” ብላችሁ ስትሰይሙን እንደው አታፍሩም?
ለማጠቃለል ትንሽ ስለ ጌቾ ልጻፍ። ጌታቸው ሽፈራው ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን ለተቸገሩ የሚራራ፣ በተለይም ለእስረኞችና ለቤተሰቦቻቸው ትልቅ ሸክም የነበረው ትልቅ ሰው መሆኑን ነው በቀረበበት ክስ ከሳሾቹ ለአለም ሁሉ የነገሩለት። እኛ በፊት እናውቀዋለን። አሁን ግን ማንን እንዳሰሩ ሁሉም አወቋል። ጌታቸው የእስረኞች ጉዳይ በጣም ይከነክንው የነበረ ነው። የእስረኞች ወዳጅ ነው።
አሁንም እኛ ከመቼዉም ጊዜ በላይ አጋርነታችንን ለጌታቸውና ለሌሎች አሁንም በወህኒ እየተሰቃዩ ላሉ የበለጠ ማሳየት ይጠበቅብናል። በተለይም የእስረኞች ልጆች ፣ አረጋዊያን እናቶቻቸውና አባቶቻቸው ዳቦ ማጣት የለባቸውም።
ግርማ ካሳNegere-Ethiopia-edtor-Getachew-Assefa-300x200.jpg

Wednesday, May 25, 2016

በዓዲ ሕርዲ የትግራይ መንግስት ኮማንዶ ልዩ ሃይል ማሰማራቱ ተነገረ

በትግራይ ክልል ቓፍታ ሑአራ ወረዳ የዓዲ ሕርዲና ዓዲ ፀፀር በሩባሳ ኣከባቢ “ለወጣቶች የቤት ማታከያ ይሰጣልና በቦታው ተገኝታቹ ተረከቡ” የሚል የመንግስት ትእዛዝ ምክንያት በቦታው የተገኙ የሁለቱ ቀበሌዎች ወጣቶች ሳያስቡት በሩባሳ ኑዋሪዎች ጥቃት ስለተፈፀመባቸው የተነሳው ግጭት የዓዲ ሕርዲና ዓዲ ፀፀር ህዝብ “የመንግስት እጅ ኣለበት፣ ህዝቡ ለማጣላት ሆን ብሎ ሰርተዋል” በማለት ከፍተኛ ቁጣ ፈጥረዋል።
የሁለቱ ቀበሌዎች ህዝብ “ህወሓት በሁሉ መስክ ኣስተዳደራዊ ዘርፎች ለኛ የሚመጥን መንግስት ስላልሆነ ከዛሬ(እሁድ 15 ጉምበት) ከቀበሌ እስከ ፌደራል ይዞብን የነበረው ውክልናችን ኣንስተናል” ብለው ኣውጀዋል።
ይሄ ውሳኔ የተላለፈው ከ15 ሺ በላይ ህዝብ ለእሁድ 14 / 09 / 08 ዓ/ም ሰለማዊ ሰልፍ ለማካሄድ እንዲፈቀድላቸው ለወረዳው ኣስተዳደር የጠየቁ ሲሆኑ ወረዳው ጥያቄው ኣግዶታል።
የሰልፉ ክልከላ ተከትለው የሁለቱ ቀበሌዎች ኑዋሪዎች ራሳቸው ስብሰባ በማካሄድ ነባር የህወሓት ታማኝ ካድሬዎች በማባረር ከህዝቡ መሃከል የራሳቸው ህዝባዊ ኣስተዳዳሪዎች መርጠዋል።
የትግራይ መንግስት ኮማንዶ ልዩ ሃይል እሁድ ሌሊት ከመቐለ ወደ ስፍራው ልከዋል።
ኮማንዶ ልዩ ሃይሉ እሁድ 15/ 09 /08 ዓ/ምሌሊት ዓዲ ሕርዲ ቀበሌ ገብተዋል።
የዓዲ ሕርዲ ና ዓዲ ፀፀር ህዝቦች “የህወሓት ውክልናችን ኣንስተናል” ከእምባስነይቲ ቀጥለው ታሪካዊ ውሳኔ የወሰኑ ተጋሩ ኢትዮጵያውያን ሆነዋል።
ህወሓት ራስዋ ስልጣኔና ራሴ የወሰድኩት የህዝብ ውክልና ለህዝቤ መልሼ ኣስረክባለው ካላለች ህዝቡ በራሱ ተነሳሽነት በኣጭር ግዜ ሙሉ በሙሉ ሊነሳት እንደሚችል ክስተቱ ኣብሪ ምልክት ነው።
የትግራይ ህዝብ ህወሓት ኣትወክለኝም ማለቱ ቀጥሎበታል።
ፎቶው የእምባስነይቲ ነው።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።

በሱዳን የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሰቆቃ!


ቅዳሜ ፡ ማያዝያ ፩ ቀን 2008 ዓም ቅፅ 16 ቁጥር 847 በጫት መቃም ወንጀል እስከ 20 ዓመት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን በሱዳን ይላል የውድ እህቴ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ዘገባ በአዲስ አድማስ እንዳነበብኩት። ግን እስረኞቹ 20 ሳይሆኑ ከ70 በላይ ናቸው በሱዳን ያሉ ከባድ ፍርደኛ ፡ከ10~20 ዓመት ፍርድ የተበየነባቸው ኢትዮጵያውያን። እኔ በኣካል እማውቃቸው እንኳን በካርቱም 51 በወህኒ ኣል ሁዳ ብቻ። በፖርትሱዳን  14 በከሰላ 1 በገዳሪፍና መደኒ ቁጥራቸው በተጨባጭ ኣላቀውም። እነዚህ ግን ከባድ ፍርደኛ ናቸው ኣስተውል 70ዎቹ ከባድ ፍርደኛ ብቻ ናቸው። በሱዳን መዲና ካርቱም ውስጥ 5 ወህኒ ቤት ኣሉ ኮበር፡ እምዱርማን፡ ሶባ፡ ደበክ እና “ኣል-ሁዳ” ይባላሉ። ወህኒ እምዱርማን የቀላል ፍርደኛ ከሁለት ዓመት በታችና ምን ይሁን ምን ፍርዳቸው ብቸኛው የሴቶች ወህኒ ነው። ኮበር፦ የፖለቲካና ከባድ ፍርደኛ እንዲሁም በሱዳን ኣራተኛው / ፖርትሱዳን፡ መደኒ፡ ኡበይድ / የሞት ፍርደኞች ማነቅያ መሳርያ ያለበት ግቢ ነው። ሶባ፦ ቀላል ፍርደኛ ከሶስት ዓመት በታችና የቼክ ማጭበርበር ወንጀል የተከሰሱ ይታሰሩበታል። ደበክ፦ ለጉልበት ስራ ሚያስፈልጉ ቀላል ፍርደኛ / ለባለ ስልጣኖች ቤት መገንብያ ” ጡብ ” ከዚሁ ነው ሚመረተው። ከከተማ ወጣ ብሎ ናይል ዳር ነው።/ ይታሰሩበታል። ወህኒ ኣል-ሁዳ ፦ በሱዳን ሃገር ውስጥ ግዙፍ ወህኒ ቤት ነው። ባለ 140 ማሰርያ ክፍሎች ያሉት……እያንድ ኣንዱ ክፍል 75 ሰው እንድይዝ 25 ኣልጋ ባለ 3 ደረጃ መላውን ክፍል የተማላለት………10500 / ኣስር ሺህ ኣምስት ሞቶ / እስረኞች እንድይዝ ተብሎ የተገነባ ነው። ይህ ወህኒ ከካርቱም ወደ ሰሜን ሱዳን ዱንጉላ መውጫ በስተ ግራ በኩል ” ሱግ ሊብያ ” ከሚባል ገበያ ማእከል ፡ እንደ መርካቶ፡ ኣለፍ ብሎ ይገኛል። በሰባት ንኡስ ግቢ እይንድ ኣንዱ በ20 ክፍል የሚገኝ ሲሆን……በተለያየ ወንጀል ከቀላል እስከ ከባድና በቼክ ማጭበርበር እንዲሁም የሞት ፍርደኞችም በውስጡ ኣቅፎ ይዘዋል። ከሱዳን በህገወጥ መንገድ ሃገሬ ገባቹ ተብሎ በሃገሪቱ ኢምግሬሽን ተከሰው ስደተኛ በመሆናቸው ብቻ ከ3000-5000 የሱዳን ፓወንድ እንዲቀጡ ኣልያም ክፍያው ከሌላቸው እስከ ስድስት ወር ታስሮ ወደ ኢትዮ፡ሱዳን ደምበር መተማ ዮሃንስ እንዲባረሩ ተወስኖባቸው ሚዳጎኑት ከዚሁ ወህኒ ነው። የሚደርሳቸው በደል ግፍ ፡ግርፍያና ዝርፍያ ከዚሁ ለመፃፍ ብሞክር ስቃያቸውን ማሳነስ ነው ሚሆነው። ምክንያቱ ተዘርዝሮ ኣያልቅም የመከራቸው ፅዋ። ባለፈው ዓመት ከተከሰተው በጣም ከባዶች ክስተት ብገልፅ እንኳን ዓርብ 3; 12; 2005 ዓም / 9; 8; 2015 እአኣ ነው። በህገወጥ መንገድ ሃገሬ ገባቹ ብሎ የከሰሳቸው ኢምግሬሽን ሱዳን የክፍያ ቅጣት ወይም የሶስት ወር ፍርድ ተበይኖባቸው ……የወርሃት ፍርዳቸው ጨርሰው ከ3 ቀን በፊት መተማ ዮሃንስ መግባት የነበረባቸው ዜጎች ……የሃገሪቱ ፓሊስ ፍርዳቸውን ከጨረሱ በሃላ እንዳይወስዳቸው የበዓል ምክንያት ኣድርጎ……ከበዓል ሳምንት በሃላ እንዲወስዳቸው ያለፍርድ መቀመጣቸው ሳይበቃ……በዚሁ ዕለት ሚያነጋ / ሓሙስ 2; 12; 2005/ 8; 8; 2013/ ለሊት መብራት ቆርጣ ስለነበር /በነገራችን ላይ ሱዳን ወህኒ መብራት መጥፋት ክልክል ነው። ካላቀረጠች በቀር……ግብረ ሶዶማውያን ስለሆኑ ነው / በእንቅልፍ እያሉ የለበሱትን ሱሪ ከስተ በሃላ በምላጭ ቀደው ለኣራት ሁኖ ሱዳኖች ደፍረዋቸው ኣደሩ። ኣንድ የኣ፡ኣ ልጅና ኣንድ የስሜን ጎንደር ናቸው።” ለክብራቸው ብየ እንጂ ስማቸው ከኔ ጋር ኣለይ ዲያሪ ውስጥ ስለምፅፈው። “” በወቅቱ ለኢትዮ፡ኣምባሳደር በካርቱም ኣቶ ኣባዲ ዞሞ ደውለን……ኢትዮጵያኖች በሁዳ ወህኒ ተደፍረዋል ስንለው………በትልቁም በትንሹም እየደወላቹ ኣትረብሹኝ ነበር መልሳቸው ……የኣምባሳደሩ። ወገን ክብሩን ተደፈረ ትንሽ ነገር ነው በሳቸው። … ሌላው፦……ሮቡዕ 13; 9; 2006 ዓም / 21; 05; 2014 እአኣ ነው……በካርቱም ህገወጥ ስደተኛ ተብለው ከ400 በላይ ኢትዮጵያኖችና ኤርትራኖች በዚሁ ወህኒ ውስጥ ታጉረዋል። ቢሆንም በወርሀ ጉንበት የሱዳን ሃገር ሙቀት ኣደለም ከወሃ ተለይተህ እንደ ኣሳ ባህር ውስጥ ብትጠልቅ ኣያረካም። መስኪኖች ሃበሻ ግን……ከሶስት ቀን በፊት ሰኞ 11; 9; 2006 / 19; 05; 2014 ለሊት ኣምጥተው በኣራት ክፍል ውስጥ / ከተሰራበት ዓቅም በላይ/ ኣጉሮው …እስከ ንጋት ሮቡዕ ያለውሃ ስለተዘጉ……ጥዋት ሮቡዕ ቆጣሪ ታረኛ መኮነን ክፍል ውስጥ ከ30 በላይ ሃበሻ / ኢትዮም፡ ኤርትራም/ ራሳቸው ስቶ ወደቆ ስላኣገኝዋቸው ………በሱዳኖች እስረኛና ኣቅማቸው ደህና የነበሩ ሃበሻ ኣሸክመው ወህኒ ግቢው ውስጥ ካለ ህክምና ለጤና እርዳታ ኣደረስዋቸው። ቢሆንም ግን………18 በቀላል እርዳታ ተሽላቸው ከግቢው ህክምና ሳይወጡ ወደ መታሰርያቸው ክፍል ሲመለሱ……3 ሃበሻ በግዜው ሂወታቸው ኣጡ። የቀሩት ወደ 12 ሚሆኑት ደግሞ ለተሻለ የጤና እርዳታ ወደ ካርቱም መሃል የሚገኘው ሆስፒታል “” መስተሽፋ ኣል-ሹርጣ “” / የፓሊስ ሆስፒታል ማለት ነው።/ በወህኒ ቤቱ ISUZ / ደፋር ትባላለች በሱዳንኛ/ ተጭነው ከተወሰዱ በሃላ …ዳግም ወደ ወህኒ ኣልተመለሱም። ተሽላቸው ወደ መተማ ዮሃንስ ይሸኙ ወይስ የሶስቱ ወገናቸው እጣ ፈንታ በነሱ ይድረስ …………… በወቅቱ ከጥዋቱ 4:00 ኣከባቢ ለኢትዮ፡ኤምባሲ ደውለን ብናስታውቅም ……የሃገራችን ኤምባሲ ሰራህተኛ በካርቱም ወገኑን ለመጠየቅ በጣም ፈጥኖ በእጁ ያለ ስራ ጥሎ……በሁለተኛው ቀን ሓሙስ 14; 9; 2006/ 22; 05; 2014 የደረሰላቸው። ይህ በየቀናትና ሳምንት ልዩነት እየተገፈፉ ከታጎሩ በሃላ የእጅ ጌጥ ካትም፡ቀለበት፡ብራስለት እንዱሁም ደህና የሆነ ጫማ ይሁን ልብስ፡ቀበቶ በዋናው ደግሞ ኪሳቸው ውስጥ ሚገኝ ጥሬ ገንዘብና ተንቀሳቃሽ ስልክ መዘረፍ ፡ መደብደብና ለሁለት ሰው በኣንድ ምላጭ መላጨት / ምላጭዋን ለሁለት ይሰጡና በኣንድዋ ገፅ ኣንተ ላጨው……ቀጥሎ የተላጨሀው ትነሳና በሁለተኛዋ ገፅ የለጨህን ወንድምህ ትላጫለህ/ ይህን ነው የሱዳን ግፍ……የኢትዮጵያ ሚድያና ውጭጉዳይ መስራቤት እህት ወንድም ሃገር የሚላት ሱዳንና ሱዳኖች። በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን ከባድ ፍርደኛ ወጣቶች ከዚሁ ወህኒ ውስጥ ናቸው። ከ10 እስከ 20 ዓመት ፍርደኛ በጫትና ሻሸመኔ / ገንጃ/ ወንጀል ተከሰው። እንዲሁም ኣንድ የሞት ፍርደኛ ጨቅላ የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ ከዚሁ ወህኒ ይገኛል። እስረኞቹ ለኢትዮጵያ ኤምባሲ በካርቱም በተደጋጋሚ የሚደርስባቸው በደል ግፍ፡ ድብደባና የስነኣእምሮ ጫና፡ የባህልና ሃይማኖታዊ ተፅእኖ እንዲሁም ቤተሰብና ወገን ከምናገኝበት ሃገራችን ቢሆንም ዝውውር ተዶርጎልን በሃገራችን እንታሰር ቢሉ……ኤምባሲው እንደ መስቀል ወፍ በየዓመቱ ኣንዴ ብቅ እያለ ምንም መፍትሄ ሳያመጣ በተከታታይ ኣራት ዓመት / 2005 ዓም ጥር ወርህ ፤ 2006 ዓም መጋቢት ኣከባቢ ፤ 2007 ዓም ግንቦትና 2008 ታህሳስ ወርሃት ላይ እየተመላለሰ ኣንዲት ቁምነጋር ሳይሰራ ማይፈፅመውን ቃል እየገበ ይጠፋል። በዞንድሮ የእስረኛ ጉብኝታቸዉ ኣቶ መሓመድ ጡፋ ፤ ዲፕሎማት ኣቶ ኣረጋ ካሳና ኣምሳሉ እንዲሁም ከኢትዮጵያን ኮሚኒትዎች ሸኽ ዳውድ እና ሌሎች የኤምባሲው ስራ ባልደረባ ሲጎበኝዋቸው……ከተሰበሰቡት እስረኛ ከፍ ያለ ወቀሴታና መፍትሄ ቢስ ስለሆኑ እንድትመጡን ኣንፈልግም በጭራሽ፡ መፍትሄ ለማትሰጡን ጉዳይ በዓመት ኣንዴ ብቅ እያላቹ በስማችን ኣትነግዱ / ምክንያቱ ወደ ወህኒ በሄዱ ቁጥር ለእስረኛ ተብሎ መዋጮ ስለሚያደርጉ…የባህል ዝግጅት ኣድርገው ገቢ ያሰባስባሉ…ከኮምኒቲው ካዝናና ከኤምባሲው ካዝና ወጪ ያደርጋሉ……ለእስረኞች ግን የመጀመርያዋ በነበረች ጉብኝታቸው በ2005ጥር ወርህ የቦንዳ ልባሽ ጨርቅና የውስጥ ነጭ ትሸርት ኣዲሶች በስተቀር ኣንዲት ቅንጣት ነገር ይዞውላቸው ቀርቦ ኣያውቁም። / የግዳስ የግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስትያን በበለጠ በዓብይ ፆም ግዜ ስካር፡ የሚበጠበጥ ጁስ፡ የሃበሻ እንጀራ ከትንሳኤ በሃላ በግድፍት ወጥ፡ በብርድ ወቅት ብርድልብስና ቅያሪ ልብሶች፡ ትሸርትና የውስጥ ሱሪ ሳይሸከሙ እስረኛ ለመጠየቅ ኣይመጡም / የኢትዮ ኤምባሲና ስሙ ብቻ የኢትዮጵያውያን የሆነ ካርቱም 3 ያለው መድህነኣለም ቤተክርስትያን ኣንድም ቀን እስረኞች ጠይቆ ኣያውቅም። ኢትዮጵያኖቹ ወጣቶች እስከ 13 ዓመት ከዚሁ ወህኒ የቆዩ ኣሉ። ከኢትዮጵያ ልዓላዊ መሬት ዓብደራፊዕና ኣልመሃል ታፍነው 20 ዓመት የተፈረዱ ኣሉ። ሁሉም ንፁሃን ከወንጀል የፀዱ ባይሆኑም ያለወንጀል ተይዘው የፍርዳቸው ክትትል የህግ ጠበቃና የቋንቋ ኣስተርጋሚ ባለመኖሩ 20 ዓመት የተፈረዱ ኣሉ። ኡ …ኡ…ኡኡ ቢሉ ሰሚ ወገን ያጡ ከኤምባሲም ይሁን ከሚመለከተው ኣካል የውጭጉዳዮች ሚኒስተር እኒህ ኢትዮጵያን ወጣት ከኣማራ፡ትግራይ፡ኦሮሞ፡ዓፋርና ደቡብ ጉራጌ ሲሆኑ………ወገኔ ብሎ ሃገራቸው ገብቶም ፍርዳቸው እንዲጨርሱ ኣለኝታ ያጡ ናቸው። ከዚሁ የሚደርሳቸው የስነኣእምራዊ፡ ሞራላዊና ሃይማኖታዊ ተፅእኖ……… ለክርስትና እምነት ተከታዮች እምነታችሁን ከቀየራቹ ወደ እስልምና ገብታቹ ቁርዓን ኣጥንታቹ ካለፋቹ እንፈታቹ ኣለን ተብለው ሶስት ኢትዮጵያን ኣስልመዋል። እንዲሁም ሌላው እነሱን ተከትሎ እንድያ ኣሰልም ብለው በእስልምና ቦጎ ኣድራጊዎች የመንግስት ኣካል ኣንዱ የሆነው “” ዴዋን ኣል ዘካ “” ሙሉ ወጪ ተደርጎላቸው በወህኒ ውስጥ ከደጅ ያሉ ሻሂ ሚሸቅጡ ሃበሻ ኣምጥቶ ድሮውላቸው……ለባለ ቤታቸው ወርሃዊ ክፍያ ይሰጣሉ ………የቀረው እንዲከተል። …ሌላው የጉሙዝ ብሄር ተወላጅ የሆኑትን ወጣት ኢትዮጵያን ……ጉሙዝ በሙሉ ሙስሊም ነው። መስገድ ኣለባቹ፡ ኣረብኛ ተማሩ ቁርዓን ኣጥኑ እያሉ በልብስና ጥቅማጥቅም እየደለሉ መላው የጉሙዝ ብሄር ተወላጅ የነበረም ያልነበረውም ሰጋጅ ኣድርጎውታል። ……ከባዱ ነገር፦ በሱዳን ውስጥ ግብረ ሰዶም እንደባህል ነው። ኣባት ልጁን ኣምኖ ከኣጎቱ እቅፍ እንዲተኛ ኣይፈቅድለትም። ይህ ሠው ግብረሰዶማዊ ነዉ ሲባል እንደምንም ማይቆጥሩት ነው። በዚሁ ኣስነዋሪ ተግባር የሱዳኖች የቀን ተቀን መመልከቱ ሰቀቀን የሆነባቸው እነዚህ እስረኞች ጭሆታቸውን ማን ይስማ። በጣም ሚያሳዝነው በዚሁ ኣስፀያፊና ኣስነዋሪ ስነምግባር ኣንድ ወገን ተብከሎብናል። የሌሎች እጣ ፈንታ ነገስ……… ይህ ወጣትስ ፍርዱ ጨርሶ ሃገሩ ሲገባ ለሌላው ትውልድ ወገን ኣለማስተላለፉ ምን ዋስትና ይኖረናል። ……ከታሰሩት ወገን የእሳላም ስጋ ስለማይበሉ ሚቸገሩትስ። ለግብፆች ኮፕቲክ ቤተክርስትያን ነግረው በሁለት ወር ወይም 3_4 ወር ሲመጡ ሽሮ ይዘውላቸው ሲመጡ የመድህነኣለም ቤተክርስትያን ግን ሂዶ ቡራኬ ለመስጠት እንኳ ፊታቸው ኣላየም። ከእስረኞቹ ስጋ ስለማንበላ ወጥ ሰርተን ምንበላበት ለእህል ወጥ የሚሆን ኣደስ ወይ ደግሞ ሩዝ ነገር ይሰጠን ብሎ ለፖሊስ ሲያመለክቱ……ኣደሱም ሩዙም ሆነ ሽንጉርቱ በሙስሊም ብር ነው የተገዛ ……ካስፈለገህ ብላ…ኣልያም ወጪህን ራስክን ቻል ተብለው ከቤተሰብ ብር እየተላከላቸው ታስረው ራሳቸውን እየከፈሉ የሚቀለቡ ኢትዮጵያን ወጣቶች የመጀመርያ ሳይሆኑ ይቀራሉ በዓለም። ኤምባሲው ግን ይህን እያወቀ ሰባእዊ መብታቸዉ ሊያስከብርላቸው ቀርቶ……እስረኛ ኣደለህም እንዴ ስጋው ብትበላው ምንችግር ኣለው ነው ያሉት። ……ጓደኛ ዘመድ ለመጠየቅ ሲመጣ ……ከተጠያቂው እስረኛ ብር ካልሰጠሀን ኣንወስድም ወደ እስረኛ መጠየቅያ ቦታ። ……ከጠያቂው ደግሞ ብር ካልሰጠሀን…ብለው ኣንተ ከወንጀሉ ሽርካ ነበርክ ኣደል……የመኖርያ ፍቃድ ወረቀትህ ግዜው ኣልፎበታል ለኢሚግሬሽን እናስክብሃለን እያሉ ብር ይዘርፈሉ……ጠያቂው ዘመድ ጓደኛ እንዲጠይቅህ እየፈለገ ምንያድርግ???………… ከራስ በላይ ንፋስ ነው። ኣንተን ብሎ እሱ ይገባል ይንገላታል ኣ ሌላው በእስረኛው ሱዳኖችና ጠባቂ ፖሊሶች ከኣቅም በላይ ዘለፋና መድልዎ ይደርሳል። ኣሁንም የእስረኞቹ ጩሀት ኣንዲትና ኣንዲት ብቻ ናት ………እባካቹ ባይሆን ሃገራችን እንድንታሰር ዝውውር ይደረግልን ነው። እኛ ከዚሁ ቁጭ ብለን ትላንት እንደሃገር ነፃነትዋን ተጎናፅፋ ራስዋን የቻለች ደቡብ ሱዳን እንኳ ዜጎችዋን በድፕሎማስያዊ ግንኝነት ዝውውር ኣድርጋ ሃገራቸው ወስዳ ለቀቀች ። በመጋቢት 2005 ከ40 በላይ ኣብሮ የነበሩ ደቡብ ሱዳኖች ሲለቀቁ። ለኛስ ወገን ሃገር የለንም?????? …በዓርብ 14; 06; 2006 ዓም/ 21; 02; 2014 እአኣ/ የሱዳን የሆነው Blue Nile BN TV የረፋዱ ኤፍ ኤም ዝግጅቱ 4:00 ላይ እንደ ኢትዮጵያን ሰዓት ……በዜና ከኢትዮጵያ የነበሩ በተለያየ ወንጀል ከተለያየ ኣከባቢ ታስረው የቆዩ ሱዳኖች በዲፕሎማስያዊ ግንኝነት ኣስመለስኩ ብሎ ዜና ሰርተዋል / BN TV ኣርቺቭ ተመልከተው በገለፅኩት ቀን/ ታድያ ለኢትዮጵያውያን ዲፕሎማስያዊ ግንኝነት ተረዳድቶ ሃገራቸው ሚያስገባ መንግስት ወገን ይጥፋ…… በተቻላቹ ድምፃቹን ኣሰሙላቸው የሃገሬ ጋዜጠኞች የኣምድ ተሳታፊዎች። ለኣሁኑ ካርቱም ወህኒ ኣል ሁዳ ያሉት ኢትዮጵያውያን የፍርዳቸው ዝርዝር ይህን ይመስላል። ወህኒ ኣል ሁዳ ያሉት ብቻ ነው እነዚህ። ስም ዝርዝራቸው ሚፈልግ ሰው ለመስጠት ዝግጁ ነይ። በድብቅ ሞባይል ስልክም ይጠቀማሉ በቪድዮ ኮል ኢሞ መገናኘት ይቻላል። በሻሸመኔ / ጋንጃ / ተከሰው 20 ዓመት የተፈረዱት 31 ወጣት ሲሆኑ…10 የተፈረዱት ደግሞ 4 ወጣት ናቸው። በጫት ተከሰው 20 የተፈረዱት 7 ወጣት ሲሆኑ 10 ዓመት የተፈረደባቸው 4 ወጣትና የኣምስት ዓመት ፍርደኛ በጫት ደግሞ ሁለት ኢትዮጵያውያን ናቸው። በሻሽመኔ / ጋንጃ / ወንጀል የተፈረዱ ጠቅላላ 35 ወጣት ሲሆኑ። በጫት ወንጀል የተፈረዱት ጠቅላላ 13 ናቸው። በጠቅላላ ከባድ ፍርደኛ 48 ወጣት ኢትዮጵያውያን በሁዳ ወህኒ ኣሉ። ኣንድ ደግሞ የሚታነቅበትን ቀን የሚጠባበቅ የሞት ፍርደኛ……ኣዋጁ ኣቅናው ሙላት የተባለ የ22 ዓመት ጨቅላ ከዚሁ ኣል ሁዳ ወህኒ ኣለ። ካስፈለገ ፎቶ ጭምርት መላክ እችላለሁ የኣዋጁ። በነገራችን ላይ……ያለፍነው ወርህ መጋቢት መጀመርያው ኣከባቢ ኣንድ ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ የሞት ፍርደኛ ኣንቀውታል። መልካሙ ታደሰ ወንድምነህ ይባላል የሱ ፎቶ ጭምርት ኣለ። ወገን ለወገን ነውና በተቻለው መጠን ጭሆታቸው እናሰማ። ባይሆን ሃገር ቤት ገብቶ ለመታሰር።

Tuesday, May 24, 2016

ሰማያዊ ፓርቲ በውስጥ ጉዳዩ ውሳኔ አሳለፈ !


በቅርቡ በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ የታየውን አጠቃላይ ችግር አስመልክቶ፤ የብሔራዊ ምክር ቤት፣ የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን እና የብሔራዊ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ፣ ግንቦት 14 ቀን 2008 ዓ.ም በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ችግሩን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
የፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሳባ፣ የምክር ቤት አባላት፣ የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን እና የስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት በተካሄደው ስብሰባ፣ በፓርቲው ውስጥ የተፈጠረው ችግር ደረጃ በደረጃ የፓርቲውን መዋቅር እና መተዳደሪያ ደንብ መሰረት በማድረግ በአስቸኳይ ችግሩ እንዲፈታ ተወስኗል፡፡
የሰማያዊ የፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች፤ ችግሩን ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በማገዝ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ የተላለፈ ሲሆን፣ ፓርቲው የሚጠበቅበትን መደበኛ ሥራ በአግባቡ እንዲወጣ ውሳኔ አሰልፏል፡፡
ግንቦት 16 ቀን 2008 ዓ.ም
Yidnekachew Kebede's photo.

ሰበር ዜና.. የብሔራዊ መረጃዉ ሐላፊ ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋርጦ መውጣቱ ተነገረ.


በትናንትናዉ እለት የወያኔ ተላላኪ ከሆኑት እና ከብሔራዊ መረጃ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ካላቸዉ ግለሰቦች መካከል አምባሳደር ቀጸላ ከብሀራዊ መረጃዉ ሐላፊ ከጌታቸዉ አሰፋ ጋር አርበኞች ግንቦት 7 በአርባ ምንጭ ላይ የወሰደዉን እርምጃ ተንተርሶ ዉይይት በሚያደርጉበት ወቅት በተመሳሳዩ በደቡብ ኢትዮጵያ ኮንሶ አካባቢ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈስሞ ከ 55 በላይ የሚጠጉ የፖለቲካ እስረኞች ማምለጣቸዉ 19 የወያኔ ታጣቂዎች መገደላቸዉና ቁስለኛ መሆናቸዉን የሚያበስር ዜና በስብሰባዉ ላይ የደረሰዉ ጌታቸዉ አሰፋ በአፋጣኝ ስብሰባዉን አቋርጦ መዉጣቱን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 በፓርላማ ዉስጥ ሳይቀር መነጋገሪያ እርእስ መሆኑን የገለጹት ምንጮቻችን አክለዉ የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የፈጠረዉ ፖለቲካዊና ህዝባዊ ጫና እንዳለ ሆኖ በጎንደር አርማጭሆ ሁመራ እና በትግራይ ጎንደር አዋሳኝ በኡማህጅር አካባቢ ድንገተኛና አደገኛ ጥቃቶች መሰንዘራቸዉን እንዲሁም በ24 እና በ25ኛ ክፍለጦር ተዉጣጪ የጸረ ሽብር ሐይል ላይ በተደረገ ሽምቅ ዉጊያ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
(ጉድሽ ወያኔ)

ሰበር ዜና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዋና ሃላፊ አቶ ኢሳይያስ ወልደ ጊዮርጊስ ከስልጣናቸው ተባረሩ።


ባሌቤታቸውም ከስራቸው የተነሱ ሲሆን፡ ሁለቱም በጸጥታ ሃይሎች ክትትል ውስጥ ይገኛሉ።በአቶ ኢሳይያስ ምትክ በደርግ ዘመን የደርግ ደህንነት የነበሩት ሃደራ አበራ ተክተዋቸዋል።ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቅርብ የነበሩት አቶ ኢሳይያስ ወልደጊዮርጊስ መባረራቸውን ተከትሎ በሌሎች ሃላፊዎችም ሆነ ሰራተኞች ላይ ስለተወሰደ ርምጃ የታወቀ ነገር የለም።ው/ሮ አዜብ መስፍን ግን የአቶ ኢሳይያስን ስንብት ተከትሎ ባለፈው ቅዳሜ አሜሪካ ገብተዋል፡ ዋሺንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ካሜራ ዕይታ ውስጥ የገቡት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአንድ ልጃቸው ጋር ሰለመጡብት ምክንያት በውል የታወቀ ነገር የለም
ምንጭ ኢሳት

ሰበር ዜና…ቴድሮስ አዳኖም ኒዮርክ ሊገባ ነው ግብረ ዓይሉም አሳፍረው ለመመለስ ተዘጋጅተዋል


የኤች አይ ቪ ኤድስ በኢትዮጵያ ላይ መከሰቱ ለሐገራችን እድገት የገቢ ምንጭ ነዉ በማለት በተቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የተናገሩት የህወሃት የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኮፐንሐገን አካባቢ ለአለም የጤና ድርጅት ሐላፊነት ለመታጨት ከአምባሳደር ቆንጂት ጋር በመንቀሳቀስ የምረጡኝ ቅስቅሳ እያደረጉ ሲሆን በአሜሪካ በተለያየ ስፍራዎች ላይ በመዘዋወር ቅስቀዉን እንደሚቀጥሉ የደረሰን መርተጃ አመልክቷል።
ቴድሮስ የተከበረዉ የግንብት 7ን ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸዉ ጽጌን ከየመን በማገት ወንጀል እጃቸዉ እንዳለት የሚታወቅ ሲሆን በወያኔ ግዞት ዉስጥ በግፍ ተላልፎ የተሰጠዉን የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ በተመለከተ በተለያየ ወቅትና ጊዜ የተዛባ መግለጫ በመስጠት ይታወቃሉ።
በተለይም በፌስ ቡክ ገጻቸዉ ላይ የተሳሳቱ የሐሰት መረጃዎችን የሚያስተላልፉት ቴድሮስ የአለም የጤና ድርጅትን እንዴት እንደተመለከቱት ለመረዳት አልችሉም ሲሉ ምሁራኖች ትችታቸዉን እየሰነዘሩ ሲገኙ ግለሰቡን በተመለከተ ከዚህ በታች የሰፈረዉን መልእክት አስተላልፈዋል።
” ዉድ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ግለሰብ በሰሞኑ በኒዉ ዮርክ ከተማ ላይ በሕገ_ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ዙሪያ እና በዚሁ አላማዉ ምክንያት ኢየዳከረ መሰንበቱ እንዳለ ሆኖ አሁን በተለየ መልኩ የአለም የጤና ድርጅት ላይ ሰንኮፉን ለመሰካት እየተፍጨረጨረ ይገኛል።
በመሆኑም በነዚሁ ወንጀለኛ የወያኔ ባለስልጣንት ምክንያት የምትወዳት ሐገርህን ጥለህ የተሰደድክ ወገን ባጠቃላይ ይህን የህዝብ ጠላት የሆነ ወንጀለኛ ግለሰብ በህዝቡና በወገኑ ላይ የፈጸመዉን አስነዋሪ ድርጊት በማጋለጥ የህዝብ አለኝታነትህን እንድታስመሰክር በኢትዮጵያ አምላክ ስም ትጠየቃለህ “።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።


ዶ/ር ታደሰ ብሩ ለአጭር ጊዜ ጉብኝት አሜሪካን ሀገር የሚገኙ ሲሆን፤ በቆይታቸው ወቅት በኢትዮጵያ የሰባዊ መብት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ዙሪያዎች ከአሜሪካን ኮንግረስማን ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በተለይም ከከሎራዶው ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማን ጋር በወቅታዊ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ አመርቂ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጾል።
ኮንግረስማን ኮፍማን ዶ/ር ታደሰን ስለ ኤርትራ ቆይታቸው ምን እንደሚመስል ጠይቀዋቸው፡- ዶ/ር ታደሰም ሲመልሱ፡- በህወሃት መንግስት የሚደረገው ህዝብን የማጣላት፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝበ መካከል በጠላትነት እንዲተያዩ የሚያደርገው ዘመቻ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸው አርበኞች ግንቦት 7 ዘላቂ ወዳጅነትን እየጠናከረ እንደሚገኝ እና የሁለቱ ህዝብ ጠላት TPLF እንጂ ሌላ መሰረታዊ ችግርች እንደሌሉ እና ለኤርትራ ህዝብ ያላቸውን አድንቆት በመግለጽ አብሮ መስራት እንደሚቻል ያላቸውን እምነት ገልጸውላቸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ የምትከተለውን የውጪ ፖሊሲዋን እንደገና እንድትመረምረውም አሳስበዋል። አያይዘውም ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማንና ሌሎች ሴነተሮች በቅርቡ በሜሪላንዱ ሴነተር ካርደን ቤንጃሚን ተረቆ የቀረበውን Resolution 432 በርካታ ሴነተሮች የፈረሙበትን የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ድጋፋቸውን ይሰጡ ዘንድ ኮንገርሰማኑን ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ኮንግረስማን ማይክ ድርጅቱ በሁለቱ ሀገራት ህዝብ መካከል እየፈጠረ ያለውን የሰላም ድልድይ እና የማቀረረብ ሂደት አድንቀው፤ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችም እንደሚከታተሉ ገልጸውላቸዋል።
Abbay media
 

Saturday, May 21, 2016

የሆላንዱ ሼር ኩባንያ በኢትዮጵያ ገመና ይፋ ሆነ


ኢሳት ዜና :- የሆላንዱ ሼር ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የአበባ አምራጭ ኩባንያ ነው። ድርጅቱ በፈርንጆች አቆጣጠር በ2004 ከኬንያ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት 1 ሺ የእግር ኳስ ሜዳ በሚያክል መሬት ላይ የአበባ እርሻ ልማት ስራ ጀምሯል። ድርጅቱ በአመት 1 ቢሊዮን 200 ሚሊዮን የጽጌረዳ አበባ ወደ ሆላንድ ይልካል። አበባዎቹን ለማሳደግ ደግሞ በእያመቱ 2 ሺ የኦሎምፒክ የመዋኛ ገንዳ የሚሞላ ውሃ ይጠቀማል። በሊትር ሲሰላ ደግሞ 5 ቢሊዮን ሊትር ውሃ ይደርሳል።
ሼር የአበባ አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ እየፈጸመ ያለውን ድርጊት ያጋለጠው በሆላንድ ታዋቂ የሆነው ዜምብላ የተባለው ዝግጅት ነው። ዝግጅቱ በኔዘርላንድ የቴሌቪዥን ጣቢያ በቀጥታ የተላለፈ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ዮስ ቫነ ዶንጀን ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ የተለያዩ ሰዎችን አነጋግሯል።
በሚስተር ፒተር ባርን ሆርን የተቋቋመው ሼር ኩባንያ 10 ሺ የሚሆኑ ሰራተኞች አሉት። የሰራተኞቹ አማካኝ ወርሃዊ ክፍያ 30 ዩሮ ወይም 750 ብር ገደማ ቢሆንም፣ ሰራተኞች ለምግብ እና ለቤት ኪራይ ከፍለው ኑሮአቸውን መግፋት እንዳልቻሉ በፊልሙ ላይ ይናገራሉ። 200 ሚሊዮን ዩሮ የሚጠጋ ሃብት ያለው ኩባንያ ለሰራተኞቹ የሚከፍለው ገንዘብ አነስተኛ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ለሆላንድ ዜጎችና ለኢትዮጵያውያን የሚከፍለው ገንዘብ ልዩነት እጅግ አስደንጋጭ መሆኑ በዘገባው ላይ ተመልክቷል። በድርጅቱ ውስጥ የሚሰሩ 42 የሆላንድ ዜጎች ወይም በመደበኛ አጠራራቸው ደቾች በአመት የሚከፈላቸው ክፍያ 9 ሺ 664 ኢትዮጵያውያን ከሚያገኙት ክፍያ በ800 ሺ ዩሮ ይበልጣል። ኩባንያው ለ42ቱ የሆላንድ ዜጎች በአመት 3 ሚሊዮን 300 ሺ ዩሮ ደሞዝ የከፈላቸው ሲሆን፣ ለቀሪዎቹ 9 ሺ 664 ት ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ደግሞ 2 ሚሊዮን 500 ሺ ዩሮ ከፍሏል።
በዘገባው ላይ የቀረበው ሌላው አስደንጋጭ ዜና፣ ኩባንያው የሚጠቀምበት የተባይ ማጥፊያ ኬሚካል ለጤና አደገኛ መሆኑ ነው። በርካታ የድርጅቱ ሰራተኞች በኬሚካሉ የተነሳ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፣ በድብቅ ካሜራ የተቀዳው ፊልምም የድርጅቱ ሰራተኞች ለአደጋ መጋለጣቸውን የሚያረጋግጥ ነው።
ኩባንያው በሚጠቀመው ውሃ ምክንያት በአካባቢው ያሉ የውሃ ምንጮች እየደረቁ መምጣታቸውን ነዋሪዎች በምሬት የሚናገሩ ሲሆን፣ ከዚህም አልፎ ድርጅቱ ወደ ዝዋይ ሃይቅ በሚልከው ፍሳሽ የተጠራቀመው ኬሚካል አሳዎችን እየገደላበቸው መሆኑን ኢትዮጵያውያን ለጋዜጠኛው ተናግረዋል።
በዘገባ ፊልሙ የተጋለጠው ሌላው መረጃ ደግሞ ከታክስ ጋር የተያያዘ ሰሆን፣ ይህ ግዝፉ ኩባንያ በፈረንጆች አቆጣጠር በ2011፣ 402 ዩሮ ወይም 7 ሺ 280 ብር፣ በ2012 ፣ 20 ሺ 201 ብር ፣ በ2013 3ሚሊዮን 137 ሺ 942 ብቻ ለመንግስት ታክስ የከፈለ ሲሆን አምናና ታች አምና ታክስ አለመክፈሉ ተጋልጧል። በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ አርሶአደሮች ተፈናቅለው የተቋቋመው የአበባ ኩባንያ፣ ለኢትዮጵያ እያስገኘ ያለው ጥቅም አነስተኛ መሆኑ በዘገባው የተመለከተ ሲሆን፣ ይህንንም ለማሳየት በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ረሃብ፣ የውሃ እጥረት፣ በልመና የሚተዳደሩ ዜጎችን ሁኔታ የባለሙያዎችን አስተያየት በማከል አቅርቧል።
ዘጋቢ ፊልሙ እንደወጣ ሼር ኩባንያ አፋጣኝ መግለጫ ያወጣ ሲሆን፣ በመግለጫው የቀረበው ዘገባ የተሳሳተ እና ኩባንያውን የማይወክል ነው ብሎአል። ከ6 ሺ ላላነሱ የሰራተኞች ልጆች ትምህርትና ህክምና በነጻ እየሰጠ መሆኑ የገለጸው ሼር፣ የዝዋይን ሃይቅ አለመበከሉንና የውሃ እጥረት እንዲፈጠር አለማድረጉን ገልጿል።
የዚህን ዘገባ ፈልም ተርጉመን የምናቀርብ መሆኑን እንዲሁም ዘገባውን የሰራውን ጋዜጠኛም ለኢሳት ቃለመልልስ ለመስጠት ፈቃደኛ በመሆኑ በቅርቡ እንደምናቀርብ ለመግልጽ እንወዳለን።

በፌስቡክ ምክንያት በርካታ ሶማሌያውያን የኖርዌይ ዜግነታቸውን ተነጠቁ


ከ1992 ዓ.ም እስከ 2000 ድረስ ባለው ጊዜ በተለያየ መንገድ ኖርዌይ ገብተው የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ አቅርበው የነበሩ ወደ አንድ መቶ የሚጠጉ ሶማሌያውያን ናቸው፤ በኖርዌይ ያገኙትን ዜግነት የተነጠቁትና የመኖሪያ ፈቃድ አግኝተው የነበሩትም እንዳይታደስላቸው እግድ የተጣለባቸው።
በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ ምክር ቤት ተመራጭ የኾኑት አቶ በሻህ ሙሴ መሐመድ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፤ ግለሰቦቹ ለኖርዌይ መንግሥት ያቀረቡት የጥገኝነት ጥያቄ፤ ሶማሌያ ውስጥ በተፈጠረው አለመረጋጋት መኖር ባለመቻላቸው መሰደዳቸውን በማስረዳት ነው። ይህ ጥያቄያቸውም ተቀባይነት አግኝቶ አንዳንዶቹ ዜግነታቸውን ካገኙ 16 ዓመታት አስቆጥረዋል። አንዳንዶቹ ደግሞ የመኖሪያ ፈቃድ አግኝተው ኑሮአቸውን ቀጥለዋል።
የኖርዌይ የፍልሰተኛ ጉዳዮች መሥሪያ ቤት፤ እነዚህ ዜጎች የዜግነቱንም ኾነ የመኖሪያ ፈቃዱን ያገኙት በሐሰት ላይ በተመሰረተ መረጃ እና ማስረጃ ነው የሚል ጥቆማ ስለደረሰው ለሁለት ዓመት ምርመራ አድርጌያለሁ ማለቱን አቶ በሻሕ ሙሴ ይናገራሉ።
“የኖርዌይ መንግሥት መረጃዎቹን አሰባሰብኩ ካለበት መንገዶች አንዱ የሰዎቹን የፌስቡክ ገፆች ነው። መንግሥቱ የአብዛኞቹን የፌስቡክ ገጾች ሲመረምር ግለሰቦቹ የጥገኝነት ጥያቄያቸውን አቅርበው በነበረበት ወቅት የሰጡት መረጃ እና ስለ እራሳቸው አሁን የሚለጥፉት መረጃ የተለያያ ኾኖ እንዳገኘውና ይህንንም መሠረት አድርጎ ተጨማሪ ማጣራት ሲያደርግ ዋሽተዋል ብሎ በማመኑ ዜግነታቸውን እንደነጠቃቸው አስታውቋል”
አቶ በሻሕ አያይዘው፤ የኖርዌይ የፍልሰተኛ ጉዳዮች መሥሪያ ቤት አገኘሁት ባለው የምርመራ ውጤት፤ አንዳንዶቹ ሶማሌያውያን ነን ከሞቃዲሾ ነው የመጣነው ብለው ጥገኝነት ጠይቀው ፌስቡካቸው ላይ የጅቡቲ እና የሌሎች ጎረቤት ሀገር ዜጎች መኾናቸውን የሚያሳይ ፎቶ ግራፍና ቪዲዮ ለጥፈዋል።
ከጓደኞቻቸውና ቤተሰቦቻቸ ጋር የተነሷቸ ፎቶዎች፣ የሚለዋወጧቸው መልዕክቶች ፈጽሞ ካቀረቡት ታሪክ ጋር እንደማይሄድ ተነግሯል። አንዳንዶቹ ደግሞ መኖር አልቻልንም ወዳሉት ሀገር ተመልሰው መሄዳቸውን መኖሪታ ቤትና ንግድቤት
መስራታቸውን የሚያሳዩ ምስሎች እና አስተያየቶች ማስፈራቸው የኖርዌይ የፍልሰተኞች ጉዳዮች መሥሪያ ቤቱ ደርሼበታለሁ ይላል።
መሥሪያ ቤቱ ይህንኑ በፌስ ቡክ ላይ የሰፈረ መረጃ ተከትሎም ምርመራ ሲያደርግ አንዳንዶቹ በጭራሽ ሶማሌኛ ቋንቋ የማይችሉና ሶማሌያ ከምትባለው አገር ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው የጎረቤት ሀገር ዜጎች ናቸው። አንዳንዶቹ ደግሞ ከሌላ ሶማሌኛ ቋንቋ ተናጋሪ ከኾኑ ጎረቤት አገራት የመጡ ናቸው። ለዚህ ደግሞ ያደረጓቸው የመልዕክት ልውውጦች እና ወደ ቤተሰቦቻቸው የላኩት ገንዘብ በማስረጃ ተያይዞባቸዋል ተብሏል።
አሁን አሁን አገራት እንደ ፌስቡክ ባሉ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ የሚውጡ ታሪኮችን እንደ የጀረባ ታሪክ ማጣሪያ መንገድ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። የዩናይትድ ስቴትስ የሠራተኛ አስተዳደር ጉዳዮች ቢሮ የተቀጣሪ ሠራተኞቹን የደህንነት ዳራ ፍተሻ ለማጥራት አዲስ ለሕዝብ ክፍት የኾኑ ማኅበራዊ ድረ ገፆች ላይ የጀመረውን ዘዴ በድረ ገጹ ላይ አስፍሯል።
አቶ በሻህ ሙሴም የኖርዌይ የፍልሰተኞች ጉዳዮች መሥሪያ ቤት ሌላ እያጣራቸው የሚገኙ ሰዎች እንዳሉ ተናግሯል። በዚህ ምክንያት ብቻ የኖርዌይ ዜግነታቸው መነጠቃቸው፣ የመኖሪያ ፈቃዳቸው እንዳይታደስ መከልከሉ እና ወደየ አገራቸው ይመለሳሉ መባሉን በመቃወም ፊርማ አሰባስበው አቤቱታቸውን ሊያቀርቡ ነው ብለዋል።
source: voa

“ጠቅላይ ሚኒስትሯን የምታስር ሀገር ዜጋ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል”


ይህንን የተናገሩት የቀድሞው የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር የአሁኑ እስረኛ ኢሁድ ኦልመርት ናቸው። ኢሁድ ኦልመርት ጠቅላይ ሚኒስትር ከመሆናቸው በፊት የኢየሩሳሌም ከንቲባ በነበሩበት ወቅት በኢየሩሳሌም ሪል ስቴት በመገንባት ከሚታወቁ ባለሐብቶች ስጦታ ተሰጥቷቸዋል ተብለው ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን በእለቱም እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል “አዎ በሪል ስቴቱ ምረቃ ላይ እንኳን ደስ አለህ ተብዬ ስጦታ ተሰጥቶኛል ስጦታው የአመራር ሂደቴን ባይቀይረውም መቀበሌ ስህተት ነበር በጠቅላይ ሚኒስተርነቴ ወቅት ለሀገሬ የተቻለኝን መስራቴን ህዝቡ ያውቃል በዚህ እኮራለሁ ጠቅላይ ሚኒስትሯን ፍርድ ቤት አቁማ ወንጀሉን መርምራ የምታስር ሀገር ዜጋ እና ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆኔ ትልቅ ኩራት ይሰማኛል ማንም ከህግ በላይ አይደለም የተፈረደብኝን ፍርድ በሙሉ እቀበላለሁ”
ኢሁድ ኦልመርት በፍርድ ቤቱ የ19 ወራት እስር ተፈርዶባቸው ከየካቲት ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን በእስር ቤት ቆይታቸውም በእስር ላይ የሚገኙ የህግ ታራሚዎችን እያስተማሩ ይገኛሉ። ሀሊም ግሊክ የተሰኙት የማረሚያ ቤት ኃላፊ ስለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የእስር ቤት አያያዝ ተጠይቀው ሲናገሩ “በጥሩ ሁኔታ ይዘነዋል ነገር ግን ከሌሎች ታራሚዎች የተለየ እንክብካቤ አይደረግለትም በእስር ቤት ሁሉም እኩል ነው” ብለዋል። የኛስ ሀገር ፍርድ ቤት የት ነው?
ኤርሚያስ_ቶኩማ‬

Friday, May 20, 2016

የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በሚቀጥለው ሳምንት ተግባራዊ የደረጋል ተባለ

በሚያዝያ ወር 2008 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ እየተተቸ ከሚገኝበት ነገር አንዱ ሐሳባቸውና የግል አመለካከታቸውን በኢንተርኔት አማካኝንት የሚገልጹ ግለሰቦችን የኢትዮጵያ መንግሥት አሥሮ የሚቀጣበት አንቀጽ ማካተቱ ነው።
ዳንኤል ብርሃኔ በኢትዮጵያ የሚገኝ የኢንተርኔት አምደኛ ነው። የራሱ ድረ ገጽም አለው። አዲሱ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ ሐሳቡን በኢንተርኔት አማካኝነት በሚገልጽ በማንኛውም ግለሰብ ላይ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ዐዋጅ ነው ብሎ ያምናል።
“ይሄ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉም ኾነ በመገናኛ ብዙሐን ሕጉ የተሰጡንን መብቶች የሚጥስ ነው። እስካሁን ካሉት ሕጎች ሁሉ የበለጠ ከልካይ ነው። በአንድ ዓረፍተ ነገር ብቻ ይከለክላል” ይላል።
የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጁ በአብዛኛው ትኩረት የሚያደርገው በኢንተርኔት አማካኝነት በሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ ነው። ነገር ግን አንድ ሰው በኢንተርኔቱና በኮምፒዩተሩ አማካኝነት ወንጀል ፈጽሟል ብቻ ሳይኾን ወንጀል ተፈጽሞበታል ተብሎ ከተገመት ያለ ምንም ፍርድ ቤት ፍቃድ እና ትእዛዝ ብሔራዊ ደሕንነት ኮምፒዩተሩን በአካል ሳይነካ እንዲመረምር ሥልጣን የሚሰጠው አንቀጽ በረቂቁ ውስጥ ተካቷል።
በኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር ዳይሬከተር የኾኑት አቶ በላይይሁን ይርጋ ረቂቅ ዐዋጁ ሐሳባቸውን በኢንተርኔት በነፃነት ከሚገልጹ ሰዎች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ይላሉ።
“አንድ ሰው የእራሱን ሐሳብና አመለካከት ከተናገረ ብቻ በወንጀል ተጠያቂ አይኾንም። የዚህ ሕግ ዋና ዓላማ ግን ሰዎች ከስም ማጥፋት ጋር በተያያዘ ለድርጊታቸው የሚኖራቸው ዓላማ ነው። ዋነኛ ዓላማቸውና ግባቸው ስም ማጥፋት ከኾነ ተጠያቂ ይኾናሉ።ም ክንያቱም ስም ማጥፋት ወንጀል ነው” ብለዋል።
ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አማካኝነት ሐሳባቻውን የሚገልጹ ግለሰቦችን በማሰቃየት፣በማሰር እና ረጅም ዓመታት በመፍረድ በተደጋጋሚ ትወቀሳለች። በዚህ ሰለባ ከኾኑት መካከል 18 ዓመት እስር ተፈርዶበት እስር ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር
ነጋ አንዱ ነው። እንዲሁም የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ከአንድ ዓመት በላይ እስር ቤት ማሳለፋቸው ሌላው ተጠቃሽ ጉዳይ ነው።
የተቀናቃኝ የፖለቲካ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባሰፈረው አስተያየት አማካኝነት ከታሠረ ስድስት ወራት ተቆጥሯል።
ሃበን ፈቃዱ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሠራተኛ ነች የኢትዮጵያ መንግሥት በፀር ሽብር ሕጉን በሀገር ውስጥ ፖለቲካው ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግ እየተጠቀመበት ነው ትላለች። የአቶ ዮናታንን ጉዳይም በምሳሌነት ትጠቅሳለች።
“በዮናታን ክስ ላይ የቀረቡት ማስረጃዎች በጣም አሳሳቢና መንግሥት አንድን ግለሰብ በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ በሚጽፋቸው ነገሮች ላይ ተመስርቶ እንዲያሥር የሚፈቅድ ነው። ዮናታን የታሠረው በጸር ሽብር ሕጉ አማካኝነት ነው። ምን አይነት ማስረጃ እንደሚቀርብበት እንኳን ሳያውቅ ነው ፍርድ ቤት የቀረበው” ትላለች።
ይሄ የኮምፒዩተር ወንጀል ረቂቅ ዐዋጅ በሚቀጥለው ሳምንት ተግባራዊ የደረጋል ተብሏል። http://amharic.voanews.com/a/3317884.html
Aud

Monday, May 16, 2016

ሰበር ዜና.. ደቡብ ኮሪያ ሲኦል ኢንቾን አየር መንገድ ላይ አራት ኢቶጵያዊያንን በቁጥጥር ስር ዋሉ።


ደቡብ ኮሪያ ሲኦል ኢንቾን አየር መንገድ ላይ አራት ኢቶጵያዊያንን በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ሶሱቱ እያንዳንዳቸዉ የአዉሮፓ እና የኢትዮጵያ የጉዞ ሰነድ የተገኘባቸዉ ሲሆን ፈትህ የሚባለዉ ግለሰብ በተለየ መልኩ ለብቻዉ በህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉር ወንጀል ተከሷል!
በደቡብ ኮሪያ አለም አቀፍ አየር መንገድ ላይ በሀገ ወጥ መንገድ ሲሸጋገሩ ሰኞ ግንቦት 01/2008 በኮሪያ የጸጥታ ሐይሎች ቁጥጥር ስር የዋሉት ኢትዮጵያዊያኑ ጉዟቸዉ ወደ አሜሪካ እንደነበረ እና እያንዳንዳቸዉ ለአሻጋሪዉ 300.000 በብር መክፈላቸዉን እንዲሁም ኢኳዶር ላይ አብሯቸዉ የሚጓዘዉ አሻጋሪ መንገድ በመቀየር ወደ ደቡብ ኮሪያ እንዳመጣቸዉ ለምንም ወደዚያ እንደመጡ እንደማያዉቁ ለደቡብ ኮሪያ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ተናግረዋል።
የወያኔን ስርአት በመጥላት ሐገራቸዉን ጥለዉ የሚሰደዱ ወገኖቻችን በመላዉ አለም ላይ እየተንገላቱ በሚገኙበት በዚህ ወቅት ላይ ደቡብ ኮሪያም ኢትዮጵያዊያንን አስራለች!
ሁኔታዉን ሲከታተሉ የነበሩ አንድ ግለሰብ ጉዳዩ እንዳሳሰባቸዉ በመጠቆም አያይዘዉ በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል አለማየህ የተባለዉ ወገናችን ወደ ሐገሩ ለመመለስ ፍቃደኛ በመሆን የመመለሻ ስምምነት የፈረመ ሲሆን ሌሎቹ አሻፈረን በማለታቸዉ ምክንያት ሶስቱም በደቡብ በኮሪያ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ቁጥጥር ስር ሲገኙ በህገ ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ወንጀል የተከሰሰዉ ግለሰብ ወዳልታወቀ እስር ቤት ተዛዉሯል።
በተያዙበት ወቅት ከፍተኛ ድብደባና ወከባ እንደተፈጽመባቸዉ የሚገልጹት መረጃዎች አጣምረዉ ከ10_15 አመት እስራት ሊያስቀጣ በሚችል ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እየተገለጸ ያሉትን ወገኖቻችንን በደቡብ ኮሪያና አካባቢዉ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን የተቻላችሁ ትብብር በማድረግ ከጎናቸዉ እንድትቆሙ ጥብቅ መልእክት አስተላልፈዋል።
ስደት ይብቃ ኑ ሐገራችንን ነጻ እናውጥ!!
( ጉድሽ ወያኔ )

በርከት ያሉ የኢህአዴግ ወታደሮች ስርአቱን በመቃወም ወደ ትህዴን ማሰልጠኛ ማእከል ተቀላቀሉ።


በዚህ ሳምንት…
በርከት ያሉ የኢህአዴግ ወታደሮች ስርአቱን በመቃወም ወደ ትህዴን ማሰልጠኛ ማእከል ተቀላቀሉ።
ከተቀላቀሉት ወታደሮች ውስጥ የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያህል፣ 1ኛ ወታደር ጥጋቡ ሞላ የደቡብ ህዝቦች ብሔር የሆነ አሁን በመከላከያ በማእከላዊ እዝ ከ22ተኛ ክፍለ ጦር ከአንደኛ ሬጅመንት ከአንደኛ ሻንበል ከጋንታ ሁለት ቲም አራት የነበረ።
2ኛ ወታደር ሙሉጌታ ሰዩም የአማራ ብሔር የሆነ ከ22ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት ሻንበል አራት ጋንታ ሶሰት ቲም አራት የነበረ፣
3ኛ ወታደር መለስ ባንቲ የአማራ ብሔር የሆነ ከሰሜን እዝ 20ኛ ክፈለ ጦር ሶሰተኛ ሬጅመንት ሻምበል አንድ የነበረ፣
4ኛ ወታደር ወልደገብርኤል ገብረሚካኤል የትግራይ ብሔር ከሰሜን እዝ 11ኛ ክፍለ ጦር ሶስተኛ ሬጅመንት የነበረ፣
5ኛ ሃምሳ አለቃ አደም ሙሃመድ የአማራ ብሔር የሆነ ከሰሜን እዝ 13ኛ ክፍለ ጦር የነበረ፣
6ኛ ወታደር ኤቢሳ አብደሰላም የአፋር ብሔር ከ25ኛ ክፍለ ጦር ሶሰተኛ ሬጅመንት አንድኛ ሻምበል የነበረ፣
7ኛ ወታደር አስማማው አፃሴ ከደቡብ ብሔረሰቦች ኦሞ ዞን ሚሊ ወረዳ ከንቲባ ቀበሌ የነበረ፣
8ኛ ወታደር አወል ሙሁዲን የአማራ ብሔር ከ25ኛ ከፈለጦር ሰድሰተኛ ሬጅመንት አንደኛ ሻምበል የነበረ፣
9ኛ ወታደር ተመስገን አግደው ከበንሻጉል ጉሙዝ ብሔር ከሰሜን እዝ ከ11ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት ሶሰኛ ሻምበል አንደኛ ጋንታ አራተኛ ቲም የነበረ፣
10ኛ ወታደር ኢሳያስ አለሊ የአማራ ብሔር ከማዕከላዊ እዝ ከ22ተኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት የመካናይዝድ ምድብተኛ የነበረ፣
11ኛ ወታደር ክፋሎም ገብረመሰቀል የትግራይ ብሔር ከ11ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት ሶሰኛ ሻምበል አንደኛ ጋንታ ሶሰተኛ ቲም የነበረ፣
12ኛ ወታደር አበበ አሸብር የአማራ ብሔር ከማእከላዊ እዝ 31ኛ ክፍለጦር አራተኛ ሬጅመንት ሰለያ የነበረ፣
13ኛ ወታደር ግርማይ ገብረሰላሴ ከትግራይ ብሔር ከማእከላዊ እዝ ከ31ኛ ክፍለጦር አራተኛ ሬጅመንት ከሁለተኛ ሻምበል አንደኛ ጋንታ አራተኛ ቲም።
14ኛ ወታደር በሽር የሴፍ የሱማሌ ብሔር የሆነ ከማእከላዊ እዝ ከ22ኛ ክፍለጦር ሰምንተኛ ሬጅመንት ሁለተኛ ሻምበል ሁለተኛ ጋንታ የሚገኝ ሆኖ ።እሱም ወደ ትጥቅ ትግል ለመሰለፍ ምክንያት ከሆኑት በጋራ ከሰጡት ሃሳብ። እኛ ወታደሮች የገዢው ሰርአት እድሜ ማራዘሚያ ከምንሆን በዚህ ወቅት አጋጥሞት ያለው የእርስ በርስ ግጭትና ቀወሰ ወደ ከፋ አደጋ ሳይወጣ ጠመንጃ ታጥቀን አገርንና ህዝብን ለማዳን የድርሻችንን ለመወጣት ተሰልፈናል ብለዋል።
አደም ሙሃመድና በሸር የሴፍ በጋራ በሰጡት ሃሳብ ደግሞ በአሁን ወቅት የአገሪቱ ወታደር ሆነህ ልትኖር አሰቸጋሪ ነው በማለትና ቀጥለውም ሰራዊቱ ለሰላም ማሰከበር የሚላከውና የሚሰጠው ማእርግና ሌሎች ግልፅ የሆነ ልዩነቶች ሰለሚያደርጉ አንድነቱ የተበታተነ በአጠቃላይ እምነት ወኔ አድሮበት በሰራዊቱ ሊቆይ የሚፈልግ የለም፣ በተለይ በአሁን ጊዚ በመላ የአገሪቱ አካባቢዎች ባሉት ግጭቶች የተነሳ በመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ጥያቄና እርሰበራሳቸው ባልተማመኑበት ሁኔታ በመድርሱ በየጊዜው ምርጫቸው ከመከላከያ ትተው ይወጡ እንዳሉ አሰታወቀ።

Saturday, May 14, 2016

በዶ/ር ቴዎድሮስ ሲመራ የነበረው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከግሎባል ፈንድ የተሰጠውን ገንዘብ ከስምምነት ውጪ መጠቀሙና ማጉደሉ ተገለጠ


ኢሳት ዜና :- የጤና ጠበቃ ሚኒስቴርን መርተው ለውጤት እንዳበቁት በመግለጥ ፣ የአለም የጤና ድርጅት መሪ ለመሆን የቅስቅሳ ስራ የጀመሩት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ ኤች አይ ቪ ኤድስንና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎችን ለመዋጋት በሚል ከግሎባል ፈንድ ለህዝብ የተሰጠውን ገንዘብ ከስምምነት ውጭ ለሌሎች አላማዎች መጠቀማቸውን የሚያመለክት የኦዲት ሪፖርት ቀርቦባችዋል።
ግሎባል ፈንድ በአውሮፓውያን አቆጣጥር በ2010 ፣ 1 ቢሊዮን 3 መቶ ሚሊዮን 35 ሺ 989 ብር ለግሶአል። ጄኔቭ የሚገኘው በምህጻረ ቃሉ GFATM የተባለው የኦዲት ተቁዋም፣ የኢትዮጰያ መንግስት ገንዘቡን ከስምምነት ውጭ እየተጠመበት መሆኑን ጥቆማ ከደረሰው በሁዋላ ባደርገው ማጣራት፣ በ88 ጉዳዮች ላይ ችግሮችን ማግኘቱን በፈንጆች አቆጣጠር ኢፕሪል 19,2012 ባወጣው ሪፖርት አስታውቆአል።
የመጀመሪያው የኦዲት ሪፖርት ከመወጣቱ በፊት ዶ/ር ቴዎድሮስ እንዲያዩት ከተላከላቸው በሁዋላ ተቃውሞ በማሰማታችው ሪፖርቱ በወቅቱ በተያዘለት ቀን ይፋ እንዳይደረግ ተደርጎአል።
ግሎባል ፈንድ ለጤና ተቁዋማት ግንባታ በሚል 24 ሚሊዮን 196 ሺ 552 ዶላር መድቦ 1 ሺ 309 የጤና ተቁዋማት የተገነቡ ቢሆንም፣ መንግስት ለመድሃኒት መግዢያ የተመደበልትን ገንዘብ ወደ ግንባታ አዙሬዋለሁ በሚል ሪፖርት በማድረጉ 57 ሚሊዮን 851 ሺ 941 ብር በላይ ገንዘብ ከስምምነት ውጭ መጠቀሙንና የድርጅቱ ኦዲተሮችም የጤና ትቁዋማቱን ደረጃ ካዩ በሁዋላ መንግስት ያቀረበውን ምክንያት ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
ኦዲተሮች ባደርጉት የመስክ ጉብኝት 165 ሚሊዮን 393 ሺ 27 ዶላር ከወጣባቸው የጤና ተቁዋማት መካከል 71 በመቶ የጤና ትቁዋማት ውሃ የሌላቸው ሲሆን፣ 32 በመቶው ደግሞ ሽንት ቤት የላቸውም። 53 በመቶው ግንባታቸው ከመጠናቀቁ ወለላቸው ተሰነጣጠቁዋል፤ 19 በመቶው ደግሞ ጣራቸው ያፈሳል። 14 በመቶው ብቻ ማይክሮስኮፕ እና የማዋለጃ አልጋዎች ያላቸው ሲሆን፣ 12 በመቶው ብቻ ትክክለኛ የመድሃኒት አቅርቦት አላቸው።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሂሳብ ሪፖርቱ 11 ሚሊዮን ዶላር ውጪ ማውጣቱን ቢገልጥም፣ ገንዘቡ ለምን ለምን እንደወጣ ዘርዝሮ ማቅረብ ባለመቻሉ ገንዘቡ እንደተበላ ተቆጥሮ ፣ ኦዲተሮች ገንዘቡ ለግሎባል ፈንድ እንዲመለስለት ጠይቀዋል።
እንዲሁም 7 ሚሊዮን 26 ሺ 929 ዶላር በግልጥ ጎድሎ በመገኘቱ መንግስት ገንዘቡን ለግሎባል ፈንድ እንዲመልስ ኦዲተሮች በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል።
ሪፖርቱ የአለም ጤና ድርጅት መሪ ለመሆን ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ላሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ አደጋን ይዞ መምጣቱን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታትሉ ሰዎች ይናገራሉ።

የዓለም አቀፉ ፍልሰት ድርጅት ታንዛኒያ 74 የኢትዮጵያ ፍልሰተኞች ወደ ሃገራቸዉ የሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻች ጠየቀ


የታንዛኒያ ኢሚግሬሽን ጉዳይ በኪሊማንጃሮ ግዛት በቁጥጥር ስር የሚገኙ 74 የኢትዮጵያ ፍልሰተኞች ወደ ሃገራቸዉ የሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻች የዓለም አቀፉ ፍልሰት ድርጅት (IOM )ጥሪ አቅርቧል።
ፍልሰተኞቹ በታንዛኒያ ዉስጥ በህገ-ወጥ ዝዉዉር ታስረዉ የእስር ጊዜያቸዉን የጨረሱ ሲሆኑ፤ የታንዛኒያ መንግስት ከ3 ሳምንታት በፊት በኬንያ ድምበር በኩል ወደ ሃገራቸዉ እንዲመለሱ ለማድረግ ቢሞክርም የኬንያ የድመበር ጠባቂዎች ኢትዮጵያዉያኑን ወደ ኬንያ ድምበር እንዳይገቡ ከልክሏቸዋል።
ፍልሰተኞቹ ወደ ኬንያ እንዲሻገሩ ታቅዶ የነበረዉ በኬንያ – ታንዛኒያ ድምበር በምትገኘዉ ታቬታ ግዛት ነበር። በግዛቱ አንድ የመንግስት ኃላፊ፣ “እነዚህ ኢትዮጵያዉያን መመለስ ያለባቸዉ ወደ ሃገራቸዉ ኢትዮጵያ እንጂ ወደ ኬንያ አይደለም፣ የታንዛኒያ መንግስት ያንን ማድረግ ሲገባዉ ወደ ኬንያ መንግስት ፍለሰተኞቹን መጣሉ ተገቢ አልነበረም” ሲሉ ለአሜርካ ድምጽ ተናግረዋል።
በታንዛኒያ የኪሊማንጃሮ ክልል የኢሚግሬሽን ኃላፊ የሆኑት ማንኩጉ እንዳሉት ኢትዮጵያዉያኑ ወደ ሃገራቸዉ ለመለስ የታንዛኒያ መንግስት በቂ ባጀት ስለሌለዉ በዳረ ሰላም የሚገኘዉ ዋና ቢሮዋችን የዓለም አቀፉ ፍልሰት ድርጅትን (IOM) እርዳታ ጠይቀዋል በማለት ለአሜርካ ድምጽ ተናግረዋል።
የፍልሰተኞቹ ጉዳይ የሚመለከተዉ በኬንያ ናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በበኩሉ ስለፍልሰተኞች ሰምቻለሁ በእርግጥ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን በማጣራት ላይ ነን ብለዋል አቶ አንዳርጉ በርሄ በኬንያ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሁለተኛ ጸሃፊ።
አክለውም፣ መረጃዉ አለን ከሞሽ ኪሊማንጃሮ አካባቢ ለነበሩት 74 ልጆች እሥራቸዉን ጨርሰዉ ወደ ኬንያ ድንበር ነዉ ዲፖርት ያደረጓቸዉ ብለዋል።
የታንዛኒያ መንግስት አሁን ምንድነዉ ግን እዝያ ችግር የነበረዉ፣ ሰዎቹ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን የሚገልጽ ሰነድ የላቸዉም፣ ሰነድ ስለሌላቸዉ እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያዉያን ናቸዉ አይደሉም የሚል ነገርም ስለ ነበረዉ፣ ሊሰፓሲ መያዝ አለበት አንድ ሰዉ ኢምባሲዉ መነገር አለበት፣ ስለዚህ ጉዳዩን እየተከታተልነዉ ነዉ አሁን ሞሽ ነዉ የሚገኙት ልጆቹ እኛጋ ፕሮሰስ ለማድረግ ደብዳቤ እንጽፋለን ሊስታቸዉን እንልካለን ብለዉ ነበረ፣ እሱን በመጠባበቅ ላይ ነዉ ያለነዉ ይላሉ አቶ አንዳርጉ በርሄ።
እንዴት ነዉ የምትለይዋቸዉ? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄም፣
“ኢትዮጵያዊ ነህ አይደለህም እንደ መንግስት የምናደርገዉ የራሳችን አሰራር አለን። ይሄ የኤምባሲዉና የመንግስት ሥራ ነዉ። ወደዝያ ሄደን ነዉ የሚናጣራዉ፣ አሁን ከእነሱ ጋር ተነጋግረናል፣ በስልክም ተደዋዉለናል። ኦፊሴላዊ የሆነ ደብዳቤ እና ሊስታቸዉን ላኩልን ባስቸኳይ ብለናቸዋል፣ እነሱም እንልካለን ብለዋል። እንግዲህ ያዉ በእነሱ አንዳንድ ነገር እየጣሩ ይሆናል የሚልኩት ከዚያም በአስቸኳይ እኛ ለመንግስታችን እናሳዉቃለን መንግስት በሚሰጠን አቅጣጫ መሰረት ከዝያ ጉዳዩን እንፈጽማለን።” ብለዋል አቶ አንዳርጉ በርሄ።
የነገሩን ቅድመ ሁኔታ ምን ያክል ጊዜ ይፈጃል? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ፣ እንግዲህ እኛ በመጣልን ሰዓት ነዉ እርምጃ የምንወስደው ብለዋል።
Voa
TPLF በአሜሪካ እሥር ቤት ላሉት ኢትዮጵያውያን ከ አሜሪካ ለማስባረር ዜግነት አይጣራም ቀጥታ የጉዞ ሰነድ ያዘጋጃል በሥቃይ ለሚገኙት ግን ዜግነት እያጣራን ነው
በኴንያ የህውሀት ጽ/ ቤት ሀላፊው አቶ በርሄ

በዲላ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መንገድ ዘግተው ፈተሻ ሲያደርጉ ዋሉ


ኢሳት ዜና :- ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጡት፣ የመከላከያ ስራዊት አባላትና የፌደራል ፖሊስ አባላት መንገዶችን ዘግተው ፍተሻ ሲያደርጉ እንዲሁም በመኪና ላይ ሆነው ቅኝት በማድረግና የሚጠርጥሩዋቸውን ወጣቶችም ይዘው ሲጠይቁ መዋላቸውን ተናግረዋል። ወታደራዊ ፍተሻውና ቅኝቱ፣ በመንግስት ታጣቂዎችና በአርበኞች ግንቦት 7 መካከል በአርባምንጭ አካባቢ የተፈጠረውን ጦርነት ተከትሎ የተካሄድ ሊሆን እንደሚችል ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ፍተሻውን እና ጥበቃውን በተመለከተ በአካባቢው ያሉ ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
Haregeweyn Abeje Iwnetu's photo.

Friday, May 13, 2016

ጦርነትን የሸሹ የመኖች ወደ ጅቡቲ ሲኮበልሉ ፣10 ሺህ ኢትዮጵያኖች ወደ የመን ይጎርፋሉ


“ታጣቂዎች አራት ኢትዮጵያዊያኖችን ገንዘብ አምጡ ብለው አይኔ እያየ ገድለዋቸዋል” የሰደተኛው ትውስታ
በሰውዲ አረቢያ መራሹ ጦር የአየር ላይ ድብደባ እና በአርሰ በርስ ጦረነት እየፈራረሰች ያለቸው ጎረቤት የመን ዜጎቿ ነፍሳቸውን ለመታደግ ሲሉ ወደ ጅቡቱ ሲሰደዱ በተቃራኒው ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያዊያኖች በአገራቸው እየደረሰባቸው ያለው የሰብ አዊ መብት ረገጣን በመሸሸሸ እና ለተሻለ ኑሮ ሲሉ እጅግ አሰከፊውን እና አሰቸጋሪዉን የበረሃ እና የባህር ላይ ጉዞ በማድረግ ወደ ሰላም አልባዋ የመን እየጎረፉ አንደሚገኙ ታውቋል።
በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የሚያተኩረው የመንግስታቱ የመረጃ መረብ(IRIN) ማክሰኞ ግንቦት 10 /2016አኤ አ ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት(2015 ) ወደ የመን ከጎረፉት 90ሺህ ሰደተኞች ውስጥ 90% ያህሉ(ከመቶው ዘጠናው እጆች) ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ሲሆን የተቀሩት ብቻ ከ ጎረቤት ሶማሊያ የመጡ ናቸው ብሏል። የኢትዮጵያዊያኑ ሰደት ዛሬም ያለማቋረጡን የገለጸው ዘገባው ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ በ 10ሺህ የሚቆጠሩ ከኦሮሚያ ክልል የወጡ ወጣት ኢትዮጵያዊያኖች በአገራቸው ውስጥ ከደረሰባቸው በደል እና መገለል አኳያ ወደ ሰውዲ አሪቢያ እና የባሕረ ሰላጤው አገሮች ስራ ፍለጋ ለመጓዝ ሲሉ ወደ ሰላም አልባዋ የመን መሰደድን መርጠዋል ፣ ከእነዚህ መካከል ከ 65 በላይ የባሕር ላይ አውሬዎች ሲሳይ ሆነዋል።
በሶማሊ ላንድ እና በጅቡቲ በኩል ወደ የመን ከተሰደዱት ኢትዮጵያዊያኖች መካከል ከ አሊቲና/ትግራይ የተሰደደው የ 31 አመቱ ከማል ፈረጃ አንዱ ሲሆን ሰኣታት የፈጀብትን የባህር ጉዞውን አጠቃሎ ከየመን ዳርቻ ሲደረሱ የተቀበሏቸው ደላላዎች/ህገወጥ አሸጋጋሪዎች ሳይሆኑ የየመን ታጣቂዎች እንደነበሩ አወስቶ በወቅቱም ሰለደረሰባቸው ግፍ እና በደል ሲዘረዝር “ ከአንዲት ጠባብ ቤት ውስጥ ለሳምንታት አሰረውን ከአገር ቤት/ከ ኢትዮጵያ ገንዘብ እንዲላክልን ለዘመዶቻችን ስልክ እንድንደውል አሰግደዱን። ገንዘብ መክፈል ያልቻሉ አራት ወገኖቻቸንን አይናችን እያየ ገደሏቸው “ሲል ሕይወቱን ብቻ ማትረፍ የቻለው ከማል አሰቀያሚው የሰደት ጠባሳውን ለኢሪን ዘጋቢ ተናግሯል።ባለቤቱን እና ልጁን ኢትዮጵያ ውስጥ ጥሎ ለተሻለ ኑሮ ወደ የመን የተሰደደው ከማል በአሁኑ ወቅት የየመኑ ጦርነት ጋብ እስኪል ድረስ የመን ወስጥ የጫት እርሻ ውስጥ በቀን ስራ በማገልገል ሰለ ስውዲ አረቢያ ጉዞው ኣና ህልሙ እየወጠነ ይገኛል።
በብዙ ሰደተኞች ዘንድ የተሻለች አገር ሆና የምትታየው ስውዲ አረቢያ በየመን ውስጥ በሚካሂደው ጦርነት ውስጥ እጆቿን በማሰገባቷ እና የየመን ሸማቂዎቹ/ሁቲዎች በበኩላቸው በጋራ ደንበሮች ላይ የፈተሻ ኪላዎችን በመቆርቆራቸው ሳቢያ የአትዮጵያዊያኖቹ ሰደተኞችም ከየመን ወደ ስውዲ አረቢያ የመሻገር እጣ ፈንታቸው የተመናመነ ሆኗል ተብሏል። ሰደተኞችን ይረዳ የነበረው የአለማቀፉ ከሰደት ተመላሶች ድርጅት (IOM) ባለፈው አመት ጥቃት ደርሶበት አምስት ኢትዮጵያዊያኖች መሞታቸውን ተከተሎ አገልግሎቱን ያቋረጠ ቢሆንም ካለፈው አመት ጀምሮ ከ 3ሺህ በላይ ሰደተኞችን ከየመን እስር ቤቶች ሰብሰቦ ወደ አገራቸው ወደ ኢትዮጵያ በፈቃደኝነት ያጓጓዘው ይሀው ድርጅት/IOM/መካከል የስውዲ አረቢያ ጉዞውን እውን ለማድረግ ከ ኦሮሚያ አካባቢ ከብቶቹን በመሽጥ ወደ የመን የተሰደደው የ 25 አመቱ አሊ አህመድ ኢብራሂም አንዱ ሲሆን አሊ ሰለ ወደፊቱ ተሰፋው ምን እንደሚያስብ ለኢሪን ዘጋቢ ሲናገር” በእውነቱ በአሁኑ ወቅት ምንም የማሰበው ነገር የለም ፣በኢትዮጵያ ውስጥ ተሰፋውም ጨልሞብኛል፣ ምናልባት የመን አንጻራዊ ሰላሟ ስታገኝ ዳግም ወደ የመን እሰደድ ይሆናል”ብሏል።
የዛሬ ስደስት ወራት ከአማራ ክልል ተነስቶ የቀይ ባህርን በማቋረጥ ወደ የመን የተሰደደው የ 40 አመቱ ኢብራሂም አሊ የሱፍ በበኩሉ የየመኑ ሰደቱ እንዳልተመቸው ፣ ስውዲ አረቢያም ብሯን እንደዘጋችበት ፣በሰነኣ/የመን የሚገኘውም የአኢትዮጵያ ኢምባሲም ጀርባውን እንዳዞረበት አምረሮ ይናገራል። በስተመጭረሻም”መሄጃው ጠፈቶን ወጥመድ ውስጥ እንገኛለን “ሲል ምሬቱን እና ሰጋቱን የገልጻል።
እኛም ብንሆን እነዚህ አገራቸውን ፣ ቤት ንብረታቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ጥለው እና ውድ እና መተኪያ የሌለው ነፍፍሳቸውን ሸጠው ለምይሳካው የሰድት ኑሮ የተዳረጉ እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ምስኪን ወገኖቻቸንን በትቻለን መጠን ልንድርሰላቸው እንደሚገባ ሊዘነጋ አይገባም ።
Tamiru Geda's photo.

የቀድሞ መንግስት ባለሥልጣናትን ያካተተ የመረዳጃ እድር አራተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ

የደርግ አባላትና መስራች የነበሩትንና በኋላም የስርዓት ለውጥ ሲፈጠር በእስር ላይ ቆይተው በቅርቡ የተፈቱት የቀድሞ መንግስት አባላት ያቋቋሙት የመረዳጃ እድር አራተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ባሳለፍነው ሳምንት በአገር ፍቅር ቲአትር ቤት አከበረ።
በአሁኑ ወቅት ወደ 280 አባላትን የያዘው ሰው ለሰው የመረዳጃ እድር የተቋቋመው በሚያዝያ ወር 2006 ዓ.ም መሆኑን የገለጹት የእድሩ ሊቀመንበር ኮሎኔል አሸብር አማረ የእድሩ ካፒታልም ከ200 ሺህ ብር በላይ መሆኑን ተናግረዋል። ኮሎኔል አሸብር የእድሩን ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ስለ አመሰራረቱ ሲገልጹ “አብዛኞቹ የእድሩ አባላት ችግርና መከራን ያለፉ ናቸው። በነበራቸው የመንግስት ኃላፊነት ምክንያት እስር ቤት ገብተው ከተፈቱ በኋላ የተቸገሩ የታመሙ እና ማረፊያ በማጣት የተጎዱ ነበሩ” ሲሉ ተናግረዋል። ሊቀመንበሩ አያይዘውም ሁለት የቀድሞ መንግስት አመራር አባላት ከእስር ከተፈቱ በኋላ መጠጊያ በማጣታቸው ጎዳና ላይ ወድቀው ሞተው ከተገኙ በኋላም የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እንደቀበራቸው ገልጸዋል። ለእድሩ መመስረትም ምክንያት የሆነው ያ ክስተት እንደሆነ የገለጹት ኮሎኔል አሸብር “ከዚህ በሀላ ለአራት እና አምስት ወራት እየተገናኘን ከተወያየን በኋላ ይህን እድር ለመመስረት ቻልን። ለእድሩ መመስረት ወንድማችን ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የተጫወቱት ሚናም ከፍተኛ ነው” ብለዋል።
በሁለት ዓመታት ውስጥ አራተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሄደው ሰው ለሰው የመረዳጃ እድር ”በእድር” ስያሜ ከመጠራቱ በፊት “ማህበር” የሚል እንዲሆን ታስቦ ለአራዳ ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ጽ/ቤት አቅርበው እንደነበረ የገለጹት ኮሎኔል አሸብር “ሆኖም ጽ/ቤቱ ማህበር ሳይሆን እድር መመስረት ትችላላችሁ ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልገውን ፎርማሊቲ አሟልታችሁ ኑ ባለን መሰረት መተዳዳሪያ ደንብ፣ የአባላት ብዛት እና በአባላት የተመረጠ አመራር ይዘን ቀርበን ከሚያዝያ 23 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ ህጋዊ እውቅና ተሰጠን” ብለዋል።
እድሩ ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስካለበት ደረጃ እስኪደርስ ድረጅ በርካታ ውጣ ውረዶችን እንዳለፈ የገለጹት የእድሩ አመራሮች በተለይ የመሰብሰቢያ ቢሮ ችግር ከፍተኛውን ችግር እንደያዘ ገልጸዋል። ኮሎኔል አሸብር “ይህን ችግራችንን የተመለከቱት ወንድማችን አቶ ጸጋዬ ወልደገብርኤል (የዩኒቨርሳል ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ባለቤት) በኮሌጃቸው እንድንሰባሰብና እንድንጠቀም ፈቀዱልን። አቶ ጸጋዬ ከዚህም በተረፈ ለ25 የእድሩ አባላት ልጆች ነጻ የትምህርት እድል ሰጥተውናል” ሲሉ ተናግረዋል። ከአቶ ጸጋዬ ወልደገብርኤል በተጨማሪ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ለ16 የእድሩ አባላት ህክምና እንደሰጠች የገለጹት ሊቀመንበሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ደግሞ 50 ሺህ ብር ድጋፍ እንዳደረገችላቸው ተናግረዋል። የእድሩ አራተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በተከበረበትበት ወቅት የደርጉ ምክትል ሊቀመንበር ሌፍቴናንት ኮሎኔል ፍሰሃ ደስታ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ተገኝተዋል።
የሰው ለሰው መረዳጃ እድር በአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በቁጥር አ/ክ/ከ/ሰ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት 930/2006 ተመዝግቦ ህጋዊ እውቅና ያለው ሲሆን 279 ኣባላት አሉት። ወቅታዊ ካፒታሉም ከ200 ኚህ ብር በላይ ደርሷል።

Wednesday, May 11, 2016

ሰበር ዜና..አል ሸባብ የኢትዮጵያን ወታደሮች ጠለፈ


13220929_1776451482587118_238412234423097300_nወደ ባይ_ዶዋ አካባቢ የተወረወሩ የአል_ሸባብ ታጣቂዎች ሶስት የኢትዮጵያን ወታደሮች አግተዉ የአል_ሸባብ ወታደራዊ ጣቢያ ( base ) ወደ ሆነው ኢል_ ቡር ( El_bur ) መዉሰዳቸዉን የሚጥቁሙ መረጃዎች ለወያኔዉ የምስራቅ እዝ ወታደራዊ ደህንነት ደርሰዉታል!
በቅኝት ላይ ተሰማርተዉ ከነበሩ ጥቂት የዝዝዉር ወታደሮች መካከል ሶስቱ መሰወራቸዉን ተንተርሶ ፍለጋ ቢደረግም ምንም አይነት ፍንጭ ጠፍቶ የነበረ ሲሆን ወታደሮቹ በአል_ሸባብ መጠለፋቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ከወደ ኢል_ቡር መንደር እንደደረሰዉ የስምሪት አዛዡን ተንተርሶ አንድ የምክትል መቶ አለቅና ሌሎች ተራ ወታደሮች መጠለፋቸዉን በሶማሌያ የኢትዮጵያዉ ጦር አዛዥ ኮነሬል የማነገብረ ማርያም ለምስራቅ እዙ አሳዉቋል።
በታህሳስ ወር 2006 እ.ኤ.አ የተመሰረተዉ አል_ሸባብን ማጥፋት ማለት መላዉ የሶማሌያን ሕዝብ ማጥፋት ማለት ነዉ! ያሉት ምንጫችን አክለዉ አል_ሸባብ ማለት እጅግ ጨካኝና አረመኔ የጥፋት ቡድን ነዉ። ከአልሸባብ ጋር የሚደረጉ ትንቅንቆች በሙሉ ከሶማሌያ ህዝብ ጋር የሚደረግ ትንቅንቆች ናቸዉ። ምንም እንኳን በዚህ በሶማሌያ ያሉት የኢትዮጵያ ወታደሮች መጠን ቢቀነስም የአል_ሸባብ ድንገተኛ ጥቃት ግን ፈጽሞ አልቀነሰም አሁን የተጠለፉት ወታደሮቻን የሚጠብቃቸዉ የከፋ ሞት ብቻ ነዉ ብለዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

በአርባ ምንጭ ያልታወቁ ሃይሎች የፖሊስ አባላትን ገደሉ


በአርባ ምንጭ ነጭ ሳር ፓርት አካባቢ ያልታወቁ ሃይሎች ከመንግስት ሃይሎች ጋር ባደረጉት ግጭት ቁጥራቸው ያልተገለጸ የፖሊስ አባላት ሲገደሉ፣ ከጣታቂዎች ወገን እንግዳ አበበ የተባለ ወጣት መገደሉን የአካባቢ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። በርካታ የፌዴራል ፖሊሶች ለህክምና ሆስፒታል መግባታቸው የተገለጸ ሲሆን፣ በከተማዋ የቤት ለቤት አሰሳ መቀጠሉም መረዳት ተችሏል።
ቅዳሜ ሚያዚያ 29 ፥ 2008 ነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርት አካባቢ በፌዴራል ፖሊሶች ላይ ድንገተኛ ጥቃት የሰነዘሩት የታጠቁ ሃይሎች፣ የአካባቢውን የፌዴራል ፖሊስ አዛዥና ቁጥራቸው ያልታወቀ ሌሎች የፌዴራል ፖሊስ አባላትን መግደላቸውን የሚገልጹት የኢሳት ምንጮች ከጥቃቱ ቀደም ባሉት ቀናትም በከተማዋ አሰሳ ሲካሄድ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በተለይ ሚያዚያ 27 ፥ 2008 ከምሽቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ በተካሄደው አሰሳ አንዲት አራስን ጨምሮ 13 የከተማዋ ነዋሪዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ከአርባ ምንጭ ተወስደው አዲስ አበባ በእስር ላይ የሚገኙት የአቶ ሉሉ መሰለ የ17 አመት ልጅም ከታሳሪዎቹ ውስጥ እንደሚገኝበትም የመጣው ዜና ያስረዳል።
በሳምንቱ መጨረሻ በነጭ ሳር ፓርክ አካባቢ ከፌዴራል ፖሊስ ሃይል ጋር ግጭት ውስጥ የገቡት ታጣቂዎች ከየት የመጡና ዓላማቸው ምን እንደሆነ በግልፅ የተገለፀ ነገር ባይኖርም፣ በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ የአርበኞች ግንቦት 7 ናቸው እየተባሉ እንደሚጠቀሱም ተመልክቷል።

Saturday, May 7, 2016

ኢሳት ዜና :- በአገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደገለጹት፣ ስዊድን እንደ ኖርዌይ ሁሉ፣ የመኖሪያ ፈቃድ ያለገኙትን ከሰኔ ወር መግቢያ ጀምሮ ለማስወጣት ማቀዷን የኢትዮጵያን የስደተኞች ሊቀመንበር አቶ ኤፍሬም አክሊሉ ተናግረዋል።
ከአገር ተገፍቶ የወጣው ኢትዮጵያዊ የመኖሪያ ወረቀት ሳያገኝ፣ መንግስት ሁሉንም ሰነዶች አዘግጅቶ የሚልክላቸው እኛን ለመሰለል ሲመጡ የመኖሪያ ፈቃድ በቀላሉ እንደሚያገኙ ተናግረዋል። ይህንን ለመቃወም በነገው እለት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

ሰበር ዜና . . በሰሜኑ ሱዳንና በወያኔ መከላከያ ሰራዊት የተደረገዉ አሰሳ አደጋ እንደገጠመዉ ጎነደር ከቋራ አካባቢ የደረሰን መረጃ ጠቁሟል።


የወያኔ ባለስልጣናቱ ሽፍታ ያሉት የጎንደር ጀግናና አርበኛ መሽጎበታል የተባለዉን ከቋራ ባሻገር የሚገኝ ስፍራ ለማሰስ ከሱዳንና ከኢትዮጵያ አቅጣጫ የተንቀሳቀሰ አሳሽ ቡድን አርበኞች አሉበት የተባለዉ ስፍራ ሲደርሱ ምንም በማጣታቸዉ ፊት ተለፊት ተገናኝተዉ ተስፋቸዉ በተመናመነበት ወቅት ድንገተኛ የመትረየስ ጥቃት ከየአቅጣጫዉ በመሰንዘሩ እርስ በእርስ እስከ መሞሻለቅ እንደደረሱ ምንጮች ከመካላከያ አሳዉቀዋል።
ከ15 ቀናት በፊት ይህን ሁኔታ ለመበቀል በንፋስ ገበያ በኩል የገቡ የሰሜን ሱዳን ወታደሮች አራት ገበሬዎችን ጠልፈዉ የወሰዱ ቢሆንም ገበሬዉ ከየአቅጣጫዉ በመነጋገር በመተናነቁ ተመልሰዉ ወደ መጡበት ፈርጥጠዋል።
የትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን የጎንደርን ገበሬ ለማሸማቀቅ እና ለማስፈራራት ከባድ መሳሪያ የጫኑ ካሚዮኖች በየመንደሩ በማንቀሳቀስ ላይ ሲገኝ አፈናዉና ድንገተኛ የቤት ለቤት አሰሳዉ ቀጥሏል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )
 

Etiopiska flyktingar i Sverige


Fredag den 6 maj kl. 13:00.
Etiopiska flyktingar i Sverige som flydde från diktaturen i Etiopien demonstrerade framför Migrationsverket i Solna. Synd att det är klämdag och ingen myndighetspersoner kom ut för att ta emot deras skrivelse och klagomål.








Thursday, May 5, 2016

ኢትዮጵያዊያንን በግፍ የገደለው አይሲስ ሶማሊያ ውስጥ አየተንቀሳቀሰ መሆኑ ይፋ ሆነ


የዛሬ አንድ አመት በሊቢያ በርሃ እና የባህር ዳርቻው ላይ 30 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቻቸንን የኢ/ኦ /ተ/ ቤ/ክ እምነታቸውን እንዲ ቀየሩ አሊያም ሞት እንደሚ ጠብቃቸው ዛቻ ቢደርባሳቸውም “ ሃይማኖታችንን በጭራሽ እንቀይረም ” በማለታቸው “ አንገታቸውን ለአክራሪው ቡድን ሰይፍ ፣ ግንባራቸውን ደግሞ ያለ ፍርሃት ለጥይት በመሰጠት እጀግ ዘገናኝ በሆነ ሁኔታ መገደላቸውን የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) በማህበራዊ መገናናዎች መሰራጨቱን ተከትሎ ኢትዮጵያዊያኖች ከዳር እሰከዳር በተለይ ደግሞ የሟቾቹ ቤተሰቦች ልባቸውን የሰበረው ያ የክፈለ ዘመናቸን የሰማእትነት ጽዋን እንዲከፈሉ ያድረጋቸው እራሱን የእስላማዊ መንግስት (Islamic State) በማለት የሚጠራው ፣ነገር ግን ፍጹም ሃይማኖታዊ እና ሰብ አዊ አስተምሮት የማይከተለው ቡድን የመሰፋፋት አድማሱን በመቀጠል ሰላም እና መረጋጋት በራቃት በጎረቤታቸን በሶማሊያ ውስጥ የእኩይ ተግባሩን እንቅስቃሲ መጀመሩን የሚያሳይ መረጃ ሰሞኑን ይፋ ሆኗል ።
ዋርካድ የተባለውን ድህረ ገጽ ዋቢ ያድረገው የ ቻይናው የሲሲቲቪ የአፍሪካ ፕሮግራም ሰሞኑን ከሞቃደሾ/ሶማሊያ እንደዘገበው ምንም እንኳን የአገሪቱ /የማሊያ መንግስት ማረጋገጫ ባይሰጥበትም የአሲስ የመጀመሪያ በሆነው የፕሮፓጋንዳ የምስል መረጃው ላይ ቀደም ሲል የ ሶማሊያው የአልሸባብ አዋጊ/ኮማደር የነበረው እና ባለፈው አመት አይሲስን መቀላቀሉ በፑንትላንድ አካባቢ መኖሩ የሚነገረለት ሺክ አብዱቃድር ሙመን ለአይሲስ አባላት “እናንተ የተመረጣችሁ ናችሁ”የሚል የሙገሳ እና የእንኳን ደህና ምጣቸሁን አቀባበል ሲያድረግላቸው በምስሉ ላይ ያሳያል። ይህ መቼ ?እና የት ቦታ ?የሚለውን የጋዜጠኝነት መጠይቆችን ለጊዜው ያልመለሰው የ አይሲስ የፕሮፓጋንዳ መረጃ በሶማሊያ ባለሰልጣናት እይታ “ሁሉንም አሸባሪዎችን እናወቃቸዋለን ፣እንጨፈልቃቸዋለን ” የሚል ምላሽ ቢኖርም በርካታ የመቋደሾ ነዋሪዎችም በተለይ ወጣቱ ክፍል ልብ ለማማለል እና ወደ ሽብር ተግባር እንዲ ገቡ ለማድረግ የተወጠነ ተራ ፕሮፓንጋንዳ ነው”የሚል ትርጓሚ ቢኖረውም ይህ ስድስት ደቂቃዎች የማይበልጠው ቪዲዮ ለአካባቢው እና ለተጎራባች አገራት ሰጋት መፈጠሩ አይቀሬ ነው ሲል ሲሲቲቪ ከመቋደሾ ዘግቧል ።
በመካከለኛው ምስራው እና በሰሜን አፍሪካ /ሊቢያ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሃይማኖት የለሹ የአይሲስ ቡድን በተመሳሳይ ወር እዚያው ሊቢያ ውስጥ 21 የግብጽ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በግፍ ማራዱን ተከትሎ ካይሮ በ አሸባሪው ቡደን ላይ ተከታታይ የአየር ላይ ድብደባ መፈጸሟ አይዘነጋም። በርካታ ኢትዮጵያዊያን በወቅቱ ምሬታቸውን እና ቁጭታቸውን በአገራቸው ውስጥ ወደ አደባባይ ወጥተው ለመግለጽ እንኳን የደረሰባቸው ወከባ ፣ግፍ እና መከራ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው።
አይሲስ በሶማሊያ ውስጥ በሚገኙት የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ጦር ሃይል ላይ ሰሞኑን ጥቃት መፈጸሙን ቢናገረም የሰላም አሰከባሪው ባለሰልጣናት ግን ዘገባውን ያሰተባብላሉ። በጎርቤት ሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አፍቃሪ አልቅይዳ እንደሆነ የሚነገርለት የሶማሊያው አልሽባብ ም ቢሆን ከሰላም አስከባሪው ጦር የሚደርሰብት ብርቱ ጥቃትን መቁቋም ባለመቻሉ ከ ገጠራማዎች ቀበሌዎች ይልቅ ብዙ ህዝብ በሚኖርበት የመቁደሾ ከተማ እና በሰላም አስከባሪው የጦር ሰፈሮች ላይ የጥቃት ሙከራ ለማድረግ መሰናዳቱን መረጃዎች ይገልጻሉ። ከኢትዮጵያ ጨምሮ ወደ 22 ሺህ የሚጠጉ የሰላም አሰከባሪ ሃይል የሰፈረባት ሶማሊያ ሰላሟ እና ደህነነቷ የተነጠላጠለው በእነዙሁ የጎረቤ ት እና ባእዳን ሃይሎች ላይ መሆኑን ተንታኞች ይናገራሉ።
ከአክራሪነት ጋር በተያያዘ ዜና በአሁኑ ወቅት በቀጠናው ውስጥ እየተሰፋፋ የመጣው ሰወዲ አርቢያ ሰራሽ ( በሺክ በእብዱል ዋሃብ ትምህርት እና በስወዲ ንጉሳዊያን ቤተሰቦች አማካኝነት ) አንደተቋቋ መ የሚነገርለት የ ወሃቢዘም አደገኛ አቅጣጫ እንዳለው በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ጥናት ያድረጉት በቀድሞው መንግስት በእርዳታ ማስተባበሪያ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ (ኮሚሽነር የነበሩት ) ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ አሰጠነቀቁ ።”የወሃቢዝም በአፍሪካ የወረራ አቅጣጫ” (The Wehabi Invasion of Africa) የሚል ሰፊ ጥናት ከስራ ባልደረቦቻቸው ጋር ማድረጋቸውን ለአሜሪካ ራዲዮ የአማሪኛ ው ከፍል ባለፈው ቅዳሜ የገለጹት ሻለቃ ዳዊት ሺያት፣ ሱኒያ የሚባሉት የ እልምና አመለካከቶች ከነብዩ መሃመድ መሞት በኋላ ተከታትለው የመጡ አንጋፋ እስተምረቶች መሆናቸውን እና የሙስሊሙ ማህበረሰብም ሊከተላቸው እንደሚገባ ጠቀሰው ፣በተቃራኒው ደግሞ የሙስሊም ወንድማማቾች Muslims Brothers Hoods)፣ሳላፊስት እና ወሃቢዛም የዘመናቸን እና የተለየ የአስተምሮት ወጤቶች መሆናቸውን ስይገልጹ አላለፉም ። አነዚህ ዘመን አመጣሻ አስተምረቶች በአብዛኛው ፖሊቲካ ዘመም መሆናቸውን ያወሱት ሻለቃ ዳዊት ለአክራሪዎቹ የእምነት አራማጆች አልቃይዳ፣ አይሲስ መሰረቾቹ ዋሃቢዝም እንደሆነ እስምረውበታል።
የሰውዲ አረቢያ የዋሂብዝም ፍልስፍና በኢትዮጵያ ውስጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ መሰፋፋቱን የጠቀሱት ሻለቃ ዳዊት የወቅቱ የአገሪቱ ገዢ መንግስት(ኢህ አዲግ) በማንኛውም ሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት የገለጹ ሲሆን ፣ይሁን እንጂ “ምናልባት አንድ የውጪ አገር በፖለቲካው ውስጥ ተጽእኖውን ለማሰረጸ ጥረት ካደረገ የመንግስት ጣልቃ ገብነት አሰፈላጊ ሊሆን ይችላል። ከዚያ ወጪ ግን ሙስሊሞች እንደ ሌሎቹ የእምነት ተከታዩች ያለ መንግስት ጥልቃ ገብነት ፣በነጻ ሊንቀሳቀሱ ፣ ያሽቸውንም ሊመርጡ ይገባል ” በማለት የግል አቋማቸውን ገልጸዋል ። በኢትዮጵያ ውስጥ ቀደምት ከሚባሉት የእምነት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የእሰልምና ሃይማኖት ተከታዮችን “ማንም ወገን ቢመጣ ሊያስተምራቸው አይችልም” ያሉት የደርግ ስር አትን እና ሰላጣናቸውን ጥለው ወደ አሜሪካ የተሰደዱት ሻለቃ ዳዊት “የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከነቢዩ መሃመድ ጀምሮ ሲወረድ ሲዋረድ የመጣውን ሃይማኖታቸውን ላለፈው አንድ ሺህ አመት በላይ በሚገባ አጣጥመው የተማሩ በመሆናቸው ምንም አይነት አዲስ አስተምሮት እና ጫና አያሻቸውም፣እንግዳ ነገር ሲመጣ ሙስሊሞች እራሳቸው ለታገሉ ይገባል እንጂ መንግስት ጣልቃ ሊገባ አይገባውም” በማለት ምክራቸውንም ለግሰዋል ። የዋሂብዝም ተከታዮች ኢትዮጵያ ውስጥ ሰለመኖራቸው ምን ማስረጃ አለ?” ለሚለው የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢዋ ጥያቄ ሻለቃ ዳዊት ሲመልሱ “ ኢትዮጵያ ውስጥ በአይኔ ያየሁት ነገር ባይኖረም ከኢትዮጵያ ወደ ፓኪስታን /ማዳራስ እንዲሁም ወደ ሱዳን እና ወደ ሌሎች አገራት ለአስተምሮቱ በመጓዝ ጥናታቸውን ሲጨርሱ ወደ ኢትትዮጵያ ለመመለስ የሚፈልጉ መኖራቸውን ሲናገሩ ሰምቻለሁ “ብለዋል።ታዲያ ችግሮችን ለማቅለል ሲባል ምን መደረግ አለበት ይላሉ ? ለሚለው ተከታይ ጥያቄ”ሁል ጊዜ ውይይት እና መመካከር ቁልፉ ሚና ይጫውታል”ብለዋል።

በቬጋስ የትግራይ ተወላጆች ብቻ የተሰብሰቡበት ስብሰባ ተበጠበጠ።


ከቬጋስ አሁን የደረሰኝ መልእክት
ሰሞኑን የብአዴንና የአማራ ክልል ባለስልጣናት በአሜሪካና አውሮፖ ተሰማርተዋል። የትግራይ ተወላጆች የሚበዙባቸውን ስለአማራው ክልል የሚመክሩባቸው ስብሰባቸውን እያደረጉ ነው። በአብዛኛው በተቃውሞ ከሽፈዋል። ስለአማራው ትግራዩ ቢመለከተው አይገርምም። አማራዎች እንዳይሳተፉ መደረጉ ግን ግራ የሚያጋባ ነው።
ቬጋስ በዚህን ሰዓት ተመሳሳይ ስብሰባ ተጠርቶ እየተካሄደ ነው። የቬጋሱ የሚለየው በስብሰባው የተገኙት በሙሉ የትግራይ ተወላጆች ናቸው። ሰብሳቢዎቹ የብአዴን ከፍተኛ ባለስልጣንና የአማራ ልማት ማህበር ሊቀመንበር ናቸው። ሌሎች እንዳይገቡ በር ላይ የተከለከለ ነው። በዚህም ግጭት ተፈጥሮ የቬጋስ ፖሊስ ደርሶ በአስለቃሽ ጢስ ለመበተን እየሞከረ ነው። አሁንም ፍጥጫው እንዳለ ነው

Wednesday, May 4, 2016

ሰበር መረጃ ወያኔ በሀገ ወጥ ሰዉ ዝዉዉር ሰንሰለት ዉስጥ !

የኢኳዶር ፖሊስ ( Ecuadorean police ) የኮሎምቢያ የጸረ አጋች ቡድን ወይም ኽዉላ ( Colombia’s elite anti-kidnapping squad, known as GAULA ) የአሜሪካዉ ሆም ላንድ ሴኪዉሪቲ ( us Home land security ) የብራዚል የህገ ወጥ ሰዉ ዝውውር ቁጥጥር ፖሊስ ( Brazilian migration police ) እና የሩቅ ምስራቅ ሀገራት ፖሊስ መረጃዎች እንዲሁም አለማቀፍ ፖሊስ ( Interpol ) በመተባበር የህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉርን ለማኮላሸት በጋራ መስራት ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል!
እነዚህ መጠነ ሰፊ አሰሳ ላይ የሚገኙት ሐይሎችን ሆም ላንድ ሴኪዉሪቲ በበላይነት ሲመራቸዉ ከእነዚህ የትብብር ሀይሎች የወጡ መረጃዎች ጣታቸዉን ወደ ሐገራችን ኢትዮጵያ ቀስረዋል አዎ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሐገራት ባለስልጣናት፣ ኢሚግሬሽን እና ቦርደር ፖሊሶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እጃቸዉ በህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉር ዉስጥ አሉበት ኢየተባለ ይገኛል።
ኢላይ ዳዊት ታደሰ ትዉልደ ኢትዮጵያዊ ሲሆን በ ( 05 May 2011 ) ኢኳዶር ላይ በእነዚህ ሐይሎች ቁጥጥር ስር ዉሏል ዳዊት ታደሰ አብዛኛዉን ንብረቱን ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚያስቀምጥና ከኢትዮጵያ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሐገራት ብዛት ያልቸዉ ስደተኞችን ወደ አሜሪካ አሸጋግሯል ዳዊት 66 የሚጠጉ አጋሮቹ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የሆሳማ ቢን ላዲን ቀኝ እጅ የሆኑ ባልደረቦችም አብረዉት ተይዘዋል ዳዊትና ግብረ አባሮቹ ( 12 March 2011 ) ለሐያሏ አሜሪካ ተላልፈዉ ተሰጥቷል።
ሰብለ አማረ ትዉልደ ኢትይዮጵያዊ ስትሆን በኮሎምቢያና በብራዚል መካከል ሀገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉር በማካሄድ ወንጀል በ 2014 በቁጥጥር ስር ዉላ በህግ ክትትል ላይ ትገኛለች በኮሎምቢያ በጥገኝነት የምትኖረዉ ሰብለ ኢትዮጵያዊ ስትሆን በህገ ወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ ኢሚግሬሽኖች ጋር በመተባበር ሰዉ እንደምታሻግር እንዱሁም ከቦርደር ፖሊሶች ጋር አብራ እንደምትሰራ መረጃዉ ያመላከተ ሲሆን በሆምላንድ ሴኪዉሪቲ ክትትል ስር ትገኛለች።
ሳራ ሳህሌ በትዉልድ ኢትዮጵያዊ ስትሆን በ 2015 በኮሎምቢያ በህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉር ወንጀል እጅ ከፍንጅ ተይዛ በቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን ከኢትዮጵያ ባለሳልጣናት ጋር ትብብር እንዳላት መረጃዎች አመላክተዋል።
ሰለሞን . . በ 2013 በብራዚል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ኢትዮጵያዊ ሲሆን የተያዘበት ወንጀል ህገ ወጥ የሰዉ ዝዉዉር ሲሆን ኢትዮጵያ ከሚገኙ ኢሚግሬሽን እና ቦርደር ፖሊሶች ጋር የተበቀ ግንኙነት እንዳለዉ መረጃዎች ሲያመላክቱ፡፤
በተያያዘ ሁኔታ ወደ እሩቅ ምስራቅ ሐገራት የሚደረጉ ተመሳሳይ ወንጀሎች በወያኔያዊያን የህግ ጥላ ተሰጥቷቸዉ ወንጀሉን በበላይነት የሚፈጽሙ አካላት ላይም ከፍተኛ ጥናት እየተደረገባቸዉ ይገኛሉ።
ባጠቃላይ ከአፍሪካ ከ18 በላይ ግለሰቦች በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረዉ በቁጥጥር ስር ለማዋል ህጋዊ ማረጋገጫ እየተፈለገባቸዉ ሲሆን አብዛኞቹ ከትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን ጋር ትስስር እንዳላቸዉ ምንጮች ጠቁመዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያነ
Gudish Weyane's photo.

በኢትዮጵያ በሕግ ሽፋን የዜጎችን መብት መጣስ ተባብሶ መቀጠሉን ሂውማን ራይት ሊግ አስታወቀ


ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ ሽብር ሕግን ከለላ በማድረግ መብታቸውን የሚጠይቁ ዜጎችን ማሰር፣ መግደልና ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን መፈጸም ተጠናክሮ መቀጠሉን የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ መብት ሊግ ገልጿል። ድርጅቱ በኦሮሚያ ክልል የበርካታ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈው ዘግናኝ እልቂት በህወሃት ኢህአዴግ መራሹ ገዥ ቡድን የተቀነባበረ መሆኑን አስታውቋል።
ይህን ኢሰብዓዊ እልቂት ተቃውመው ለመብታቸው የታገሉት ከ 22 በላይ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች የሃሰት ክስ እንደተመሰረተባቸው አመልክቶ ፣ በህወሃት የተቀነባበረ ሴራ በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ካለ ፍትሕ በእስር ቤት እየማቀቁ ነው ብሎአል።
በኢትዮጵያ ያለው የፀረ ሽብር ሕግ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን በሚጻረር መልኩ የወጣ ሲሆን ይህም የዜጎችን የመጻፍ፣ የመናገርና የመቃወም ሕገ መንግስታዊ መብቶችን በሚጥስ መልኩ ሆን ተብሎ ተረቆ በሥራ ላይ መዋሉን አስታውቋል።
በኦሮሚያ የተነሳውን ሰላማዊ የዜጎችን ጥያቄ በመደገፍ ከሕዝባቸው ጋር በመሆን ሲቃወሙ ከነበሩት ውስጥ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፣ የፓርቲው ፀሃፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አዲሱ አቡላና ሌሎችም በፈጠራ የሽብር ክስ መከሰሳቸውንና የመብት ጥሰቱ ተባብሶ መቀጠሉን ሪፖርቱ አመላክቷል።
መብታቸውን በመጠየቃቸው ብቻ በሽብር ሕግ ስም አላግባብ ታስረው የሚገኙ ንጹሃን ኢትዮዮጵያዊያንን ህወሃት መራሹ መንግስት ካለ ምንም ቅድመ ሁኔታዎች ክሳቸውን በማንሳት ሊፈታቸው ይገባል ብሎአል።

Tuesday, May 3, 2016

ሰበር ዜና —4 የህወሃት ብሄራዊ መረጃ ከፍተኛ ሚስጥራዊ አባላት ተገደሉ


የብሔራዊ መረጃ የቅድመ ዝግጅት ማሰራጫና ማከናወኛን ክፍል መሰረት ባደረገ መልኩ ለመረጃ ክፍሉ ሐገር ለሐገር እየተዟዟሩ ሲሰልሉና ወሬ ሲያቀብሉ እንዲሁም ያለአግባብ ወገኖቻችንን ሲያሳስሩና ሲያስገድሉ የነበሩ አራት ቁልፍ የህወሃት ደህንነት አባላቶች መገደላቸዉን ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። ተጠሪነታቸዉ ለመረጃዉ ክፍል ዳይሬክተር ብቻ እና በከፍተኛ ሚስጥር ከሌሎች አባላት እንኳ በተሰወረ መልኩ የሚንቀሳቀሱ ብዛት ያላቸዉ አባላቶች ላይ እርምጃዎቹ ያነጣጠሩ ናቸዉ ሲሉም ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን እርምጃ የተወሰደባቸዉ ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ከዚህ በታች አስቀምጠዋል ።
1. አቶ በኩር ባዘዘዉ ገብረህይወት
2. ቀሲስ ትንሳኤ ሃይለ መለኮት
3. ሲስተር ሳምራዊት በቃሉ
4. መምህር ጣፋ አጋፋሪ
በየካቲት 28/2008 ለመረጃዉ ክፍል የወረደዉ የሞት መርዶ ብዙዎችን ያስደነገጠ ከመሆኑን ባሻገር የአራቱም ግለሰቦች አሟሟት በተመሳሳይ ወቅትና በተለያየ ክልል መሆኑ እንዲሁም አራቱም ከተገደሉ በኋላ ለመረጃ ክፍሉ ካልታወቁ ግለሰቦች የስልክ ጥሪ ተደርጎ በሐገሪቷ ላይ እየተካሄደ ያለዉ አፈናና ግድያ እስካልቆመ ድረስ እርምጃዉ እንደሚቀጥል ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ ዉጥረቱን አባብሶታል።
በተለይም በኦሮሚያ ክልል እና በጎንደር እንዲሁም በኦጋዴን ክልል አካባቢ ተሰማርተዉ የነበሩ የመረጃዉ ክፍል ሰራተኞች በሙሉ እርምጃ ሊወሰድባቸዉ እንደሚችል የጠቆሙት ምንጮቻችን በእነዚህ ክልል የተሰማሩ አባላቶች ጠርገዉ እየወጡ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል ብለዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

በኢትዮጵያና ሶማሊያ ድንበር አካባቢ በተነሳ ግጭት 10 ሰው ሞተ


በቅርቡ በኢትዮጵያና የሶማሊያ የድንበር አካባቢ ከአስር ለሚበልጡ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ግጭት ተከትሎ የሁለቱ ሃገራት ተወካዮች በጅጅጋ ከተማ በመምከር ላይ መሆናቸው ተገለጠ። በኢትዮጵያ የሚገኙ ልዩ ሃይሎች በየጊዜው ከሶማሊያ አርብቶ አደሮች ጋር የሚያደርጉት ግጭት በድንበር ዙሪያ ያለውን የፀጥታ ሁኔታ ስጋት ውስጥ እንዳካተተው የሶማሊያ ባለስልጣናት ለመገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል። የሶማሌ ክልል መስተዳደር ባለስልጣናት በቅርቡ ለተፈጸመው ከ10 በላይ የሶማሊያውያን ግድያ የአል-ሸባብ እጅ አለበት ቢሉም የሃገሪቱ የጋልሙዱግ ግዛት ተወካዮች ግድያውን በታጣቂ ሃይሉ ሳይሆን በኢትዮጵያ ልዩ ሃይሎች መፈፀሙን እንዳስታወቁ የሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በሁለቱ ሃገራት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎም የሶማሊያው የጋልሙዱግ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አብደልካሪን ሁሴን ሌሎች የፀጥታ ሃይሎችን በማካተት ከኢትዮጵያ ተወካዮች ጋር እየመከሩ መሆኑም ታውቋል። በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ቆይታም በድንበር ዙሪያ በተደጋጋሚ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እልባት ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ ሃላፊው አክለው አስረድተዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት በየጊዜው ድንበርን በመጣስ ወደ ሶማሊያ ለመዝለቅ የሚያደርጉት እርምጃ በድንበሩ አካባቢ የጸጥታ ስጋት ፈጥሮ መገኘቱን የተለያዩ አካላት ይገልጻሉ። የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮቹን በአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ሃይል ስር አሰማርቶ ቢገኝም በተለያዩ ጊዜያት የተናጥል ወታደሮችን ወደሶማሊያ በማስረግ ከአልሻባብ ጋር ውጊያን እንደሚያካሄዱም የሶማሊያ ባለስልጣናት ሲገልጹ መቆየታቸው ይታወሳል። ይሁንና ወታደሮች በድንበር በኩል የሚያደርጉት ጉዞ ከአርብቶ አደሮች ጋር ግጭት ውስጥ እየከተታቸው መሆኑንም ለመረዳት ተችሏል።

ከአውሮፓ ኢትዮጵያ ኑሮውን ለማድረግ የገባው ወጣት በሳንጃ ተወግቶ ተገደለ


በፈትያ አንዋር
ዓመት በዓል ከመድረሱ ሳምንት በፊት ጀምሮ የተለያዩ ውክቢያዎች፣ ፈንጠዚያዎች እንዲሁም ደስታና ሳቅ፣ በሌላ ጎኑ ደግሞ ሀዘንም ሊኖር እንደሚችል እሙን ነው፡፡
ባሳለፍነው የፋሲካ በዓል ዋዜማም በጣም አስደንጋጭ ነገር ተፈጥሯል፡፡ መቼም ሰው ነንና በበዓል ዋዜማ ደስታችንን ለመግለፅ ወደተለያዩ መዝናኛ ቦታዎች ማምራታችን የማይቀር ነው፡፡ በዋዜማው በአዲስ አበባ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም ውስጥ ሁለት የዛው አካባቢው ነዋሪዎች ሊዝናኑ በወጡበት ባልታሰበ ፀብ በሳንጃ የአንደኛው ሰው ሕይወት ሲያልፍ ሌላኛው ደግሞ ሳንባው ተወግቶ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምንና ላይ ይገኛል ፡፡