ጎንደር የወያኔ ስርዓትን ጭንቅ ውስጥ እንደከተተችና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ሰሜን ጎንደር በጠላት እጅ መውደቋን አመራሩን ዋና የችግሩ መንስኤ አድርጎ የቆጠረ ስብስባ በጎንደር ከተማ እየተደረገ እንዳለና የህውኃት ከፍተኛ መኮንኖች ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ አስተማማኝ መረጃዎች አሰታወቁ፡፡
በስብሰባው ሳሞራ የኑስን ጨምሮ ሌሎች ወታደራዊ መኮንንኖች የተገኙበት ነው ተብሏል፡፡ ከተማዋም ከፍተኛ የወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በብዛት አየተንቀሳቀሱ መሆኑን ምንጫችን ገልፆልናል፡፡
**
በሚያዚያ 21-28/2009 ዓ/ም በጎንደር ከተማ የሚከበረው የከተሞች ፎረም ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን በአሉንም አናከብርም የሚል ይዘት ያለው ፁሁፍ ወረቀት እንደተበተነ የተበተነውን ወረቀት ያዪ የአየን እማኞች ገልፀውልናል።
ለመሆኑ የከተሞች ፎረምና በዐል እነ መቀሌ ያክብሩት እንጂ ለ26 አመት ሆነ ተብሎ እንዳታድግ ለተደረገችው ጎንደር ከተማ ምኗ ነው፡፡ ጎንደር ላይ ባለፉት አመታት ምንስ ሰራን ብለው ሊያስጎበኙ ይሆን ለሚመጡት እንግዶች ነው ወይስ በዐሉ ጎንደርን ላለፉት 26 አመት እንዴት እንደገደሏት በተግባር ልምድ መቅሰሚያ ከተማ መሆኗን ሊያሳዯት፡፡ የወያኔ የለበጣ ስላቅ አያልቅም መቸም!
No comments:
Post a Comment