በጎንደር ከተማ በቀበሌ 15 ቀጠና 1 ፋሲለደስ እስታዲየም አካባቢ ነዋሪ የሆነው የሆነው የህውሀት የሰሜን ጎንደር ፣ የደቡብ ጎንደር ፣ የምእራብ ጎጃም የአካባቢው ማለትም የቀጠናው የህውሀት ሰብሳቢ ሊቀምንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ሊቀመንበር የሆነው አምባየ አማረ በተባለው ግለሰብ ሚያዚያ 12 ቀን 2009 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡47 ሰዓት ሲሆን መኖሪያ ቤቱ በቦምብ ጥቃት ተፈፅሞበታል ፡፡
ይህ በንዲህ እንዳለ በትላንትናው እለት በጎንደር የተፈጠረውን ችግር ለማረጋጋት ከሙሴ ባምብ ወታደራዊ ካምፕ ወታደር ጭኖ የተንቀሳቀሰ አንድ ኦራል መኪና ምሽት 4፡40 ላይ ልዩ ስሙ የኢትዮጵያ ካርታ የሚባለው ቦታ ላይ በጥይት ተመትቶ መኪናው ሲገለበጥ 4 ወታደሮች ወዲያውኑ ሲሞቱ 5 ቀላል ቁስለኛ ሆነዋ ኦራል መኪናው ዛሬ 13/08/2009 ከቀኑ 5 ፡ 00 ሰዓት ተጎትቶ ወደ ጎንደር አዘዞ ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ የመጣ ሲሆን የቆሰሉ ወታደሮች አዘዞ በሚገኘው የጦሩ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ ሟቾችም አዘዞ ሎዛ ማሪያም ቤ/ክርስቲን ተቀብረዋል፡፡
No comments:
Post a Comment