ዳግማዊ ተሰማ

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በፊት የቀድሞ የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ሃላፊና የምክር ቤት አባል የነበረው ዳግማዊ ተሰማን እኔ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ አናንያ ሶሪ፣ ሃብታሙ ምናለና ፍቃዱ በቀለ ካዛንቺስ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ጠይቀነው ነበር።

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በፊት የቀድሞ የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ሃላፊና የምክር ቤት አባል የነበረው ዳግማዊ ተሰማን እኔ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ አናንያ ሶሪ፣ ሃብታሙ ምናለና ፍቃዱ በቀለ ካዛንቺስ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ጠይቀነው ነበር።
ዳግምም “ከታሰርኩ ዛሬ ሳምንቴ ነው። እስከዛሬ ማንም ያነጋገረኝ አካል የለም። ስም፣ አድራሻዬንና የትምህርት ደረጃዬን ብቻ ነው የተጠየኩት። ኮማንድ ፖስቱ ገና አልተደራጀም ተብያለሁ። ጠፍተህ ከርመሃል…’ ከመባል ወጪ ለምን እንደታሰርኩ እንኳን በዝርዝር አላውቀውም። ከምኖርበት ኦሎምፒያ አከባቢ ግን በርከት ያሉ ልጆች ታስረዋል።” ብሎናል።
ያው የመጠየቂያው ደቂቃ በጣም ትንሽ በመሆኑ ብዙ ነገር መነጋገር ሳንችል ቀርተናል። ከፖሊስ ጣቢያው ቅጥር ግቢ ያለው የጸሐይ ሙቀት ደግሞ አይጣል ነው። ጸሐይቷ እንኳን ቀዝቀዝ ብትል ምናለበት ….
No comments:
Post a Comment